Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Friday, May 3, 2013

ሦስት:- ደፋርና ጭስ መውጫ አያጣም! የኢትዮጵያ ሳታላይት ቴሌቪዢንና ራድዮ



እስካሁን ድረስ ያሳየነው ችሎታ የማጥፋት ወይም የማክሸፍ እንጂ አዲስ ነገርን ወይም አዲስ ሥርዓትን የመፍጠር አይደለም፤ በአለፉት ሃምሳ ዓመታት ውስጥ ቢያንስ ሦስት የአስተዳደር ሀሳቦች መቅረባቸውን አውቃለሁ፤ አንዱ በአቶ ሀዲስ አለማየሁ፤ ሁለተኛው በኤንጂኒር-የሕግ ባለሙያ ደመቀ መታፈሪያ፣ ሦስተኛው የኔ ናቸው

አእምሮአቸውና ልባቸው በማርክሳዊ-ሌኒናዊ ጦር ተቀስፎ የተያዘባቸው ወጣቶች ሌላ ሀሳብን የማይሰሙበት ጊዜ ነበር፤ ማርክሳዊ-ሌኒናዊ ጥራዝ-ነጠቅነት ብቻ የሁሉም ዓይነት የእውቀት ምንጭ ብለው በጭፍን የሚያምኑ ወጣቶች በተለይም ከኢትዮጵያዊ የፈለቀ ሀሳብን ለማጥላላት ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን አይቆጥቡም ነበር፤ የሌኒን የጡት ልጆች እርስበርሳቸው ተፋጁና ያሸነፉት ዛሬም ከፋፍለው ይገዙናል፤ የት እንደሚያደርሱን ገና አላወቅንም።

ሁለት፦ ደፋርና ጭስ መውጫ አያጣም! የኢትዮጵያ ሳታላይት ቴሌቪዢንና ራድዮ: By መስፍን ወልደ ማርያም



ልክ ወያኔ/ኢሕአዴግ የኢትዮጵያን መገናኛ ዘዴዎች ሁሉ ለአንድ የወያኔ ዓላማ ብቻ እንዲውል እንዳደረገው ኢሳትም የኢትዮጵያን ሕዝብ ለአንድ ቡድን ዓላማ ተገዢ ለማድረግ የታሰበ ነው የሚሉ ሰዎች አሉ፤ እስቲ ማስረጃ ቁጠሩ ሲባሉ ከስሜትና ከጥርጣሬ በቀር ምንም ተጨባጭ ነገር አይወጣቸውም፤ የተለያዩ ቡድኖች፣ በትጥቅ ትግል ውስጥ ነን ከሚሉ ጀምሮ በሰላማዊ የፖሊቲካ ትግል ተወስነናል የሚሉና በተገኘው በማናቸውም መንገድ ወያኔ/ኢሕአዴግን እንታገላለን የሚሉ ሁሉ በኢሳት መድረክ እንዳገኙ ይታያል፤፤
 
ኢሳት የራሱ የፖሊቲካ እምነት የለውም፤ ወይም ሁሉንም የፖሊቲካ እምነቶች ይደግፋል ማለት ይቻል እንደሆነ አላውቅም፤ ዝም ብሎ እምነት የሌለው መድረክ ነው እንዳይባል ወያኔን ተቃዋሚነቱ ጎልቶ የወጣ ነው፤ ኢሳት የጸዳ የዴሞክራሲ መድረክ ነው ከተባለ ጸረ-ዴሞክራሲ አቅዋም ያላቸውን፣ ወያኔንም ጨምሮ ማስተናገድ የሚኖርበት ይመስለኛል፤ ይህ ግን ጎልቶ እየታየ አይደለም።

አንድ ፦ ደፋርና ጭስ መውጫ አያጣም! የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዢንና ራድዮ: By መስፍን ወልደ ማርያም

በአለፉት ሠላሳ ዓመታት በኢትዮጵያ የለውጥ እንቅስቃሴ ላይ እንደኢሳት (የኢትዮጵያ ሳታላይት ቴሌቪዥንና ራዲዮ) ያለ ኃይል የትኛውንም የኢትዮጵያ አገዛዝ አጋጥሞት አያውቅም፤ በመሠረቱ የኢሳት መሣሪያነት ከባህል ውጭ ቢሆንም የባህል ይዘት አለበት፤ ይህንን ወደኋላ አመለክታለሁ፤ ወደድንም ጠላንም የኢትዮጵያ ታሪክ በመሠረቱ ሁሌም በኃይል ላይ ቆሞ በኃይል የሚሽከረከር ነው::  

በአለፉት አርባ ዓመታት ውስጥ የመጡት አብዮተኞች ሁሉ ይህንን በመሠረታዊነት የመክሸፍ ምንጭ የሆነውን የጉልበት አምልኮት እንደዓላማም እንደመሣሪያም ይዘው የተነሡ ናቸው፤ ዛሬም ቢሆን ተሸናፊዎችም ሆኑ አሸናፊዎች አብዮተኞች የሚያወሩትና የሚጽፉት ከጉልበተኛነት ከረጢታቸው ሳይወጡ ጥፋታቸውን እንደልማት፣ አላዋቂነታቸውን እንደብልህነት በማድረግ ራሳቸውን አታልለው ሌላውን ለማታለል እየሞከሩ ነው::

የእነአንዱአለም እና እስክንድር ነጋ ነገር በጠቅላይፍ/ቤት (ወሰንሰገድገብረኪዳን)

ሰበር ዜናውን ከስፍራው የዘገበው ጋዜጠኛ ወሰንሰገድ ገብረኪዳን፤ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የነበረውን የችሎት ሂደት በዝርዝር ዘግቧል። ከዚህ ቀጥሎ እናቀርባለን። 

“ሀገሬን ሀገሬን – የምትል ወፍ አለች
እኔን እኔን መስላ፣ ታሳዝነኛለች”
– አዝማሪ

 ሌሊት ሌሊት እንደ “ዳዊት ደጋሚ” ስለማመሽ ጠዋት ጠዋት ተጋድሜ ማርፈድ ልማዴ ነበር፡፡ ዛሬ ዕለተ ሐሙስ ሚያዝያ 26 ቀን 2005 ዓም፣ ካለወትሮዬ በጠዋት ከዕንቅልፌ ተነሳሁ፡፡ እናም ወደ ጠቅላይ ፍ/ ቤት አመራሁ።ዕለቱን እያሰብኩ፡፡

! …… ከ ፍሰሓ ደስታ ጋር ማወዳደር ! ለምን? ……!



በተወሰኑ ካድሬዎች (በትግርኛ) ተፅፎ የኣብርሃን ፅሑፎች ይቃወማሉ ተብለው ለታመነባቸው ፌስቡከኞችና ለህወሓት ኣባላት የተበተነው ፅሑፍ ኣይቸዋለሁ። ፍሬ ሓሳቡኣብርሃ ደስታ ልክ እንደነ ፍሰሃ ደስታ የራሱን ክብር ኣሳልፎ ለመስጠት፣ ቤተሰቡና ሀገሩ ለመሸጥ ከትግራይ ጠላቶች ኣብሮ እየተንቀሳቀሰ ሲሆን ተጋሩ ግን ……” የሚል መልእክት ኣለው:: ይሄንንግብረ መልስየተሰጠው ሰው በተግባሩ (በሰራው ስራ) እንጂ በዘር ሀረጉ፣ በሃይማኖታዊ እምነቱና ፖለቲካዊ ኣመለካከቱ ሊመዘን ኣይገባምየሚል መልእክት ያለው ሓሳብ በመፃፌ ነው።

ይሄንን ታድያ የኣንድ ህዝብ ክብር ኣሳልፎ መስጠት ኣይደለም። የሰው ክብር ያለው ሰው በመሆኑ ላይ ነው። ሰው እንደሰው መከበር ኣለበት፤ ሌላው ሁሉ የግል ጉዳይ ነው። እኔ የመሰለኝን ሓሳብ ስለፃፍኩና ሌሎችን ሰዎች (ማናቸውም ከትግራይ ወይ ኢትዮዽያ ወይ ኣውሮፓ ወይ የትም) የኔን ሓሳብ ቢጋሩ እንዴትክብርን ለሌሎች ኣሳልፎ  መስጠትሊባል ይችላል? እኔ ሀገር ለመሸጥ ኣልተነሳሁም።  

Tuesday, April 30, 2013

ጎዳና ተዳዳሪው የወታደራዊ መረጃ ኮሎኔል

እንደ አለመታደል ሆኖ ከቅርብ የታሪካችን ዘመን እንኳን ብንነሳ ተጠሪነቱ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ብቻ የሆነ፣ ብሔራዊ ስሜት ያለው፣ ጠንካራ የሆነ ሕዝባዊ መሠረት ያለው የመከላከያ ኃይል ለመፍጠር እየተደረገ የነበረውና አሁንም እያየነው ያለው ሙከራ መንግሥት በተለዋወጠ ቁጥር ሂደቱ የሚንገዳገድና የሚገታ ነው፡፡

በአገሪቱ ዘመናዊ የመከላከያ ኃይል በመገንባት ረገድ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ያደረጉት ጥረት ከኢትዮጵያ አልፎ አፍሪካና ኮርያ ልሣነ ምድር የዘለቀ ብቃቱንና ጥንካሬውን ያስመሰከረ፣ የኢትዮጵያዊነት ከፍተኛ ስሜት፣ ኩራትና ወኔ ያለው የመከላከያ ኃይል ሠራዊት ሊፈጥሩ መቻላቸውን የታሪክ ድርሳናት ይመሰክራሉ፡፡