Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Sunday, March 31, 2013

ከቤንሻንጉል አማርኛ ተናጋሪ ዜጎችን በግፍ የማፈናቀሉ ተጠናክሮ ቀጥሏል

-ጥቃቱ ህፃናትና አረጋውያን ላይም እየደረሰ ነው
አማርኛ ተናጋሪውን ከየቦታው የማፈናቀሉ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የመረጃ ምንጮቻችን አስታወቁ፡፡ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች እንደሚሉት በዚህ ሳምንት ውስጥ ብቻ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከማይ ዞን ያሶ ወረዳ 25 ሺህ አማርኛ ተናጋሪዎች እየተደበደቡ በጭነት መኪና ተጭነው ከመኖሪያቸው ተባረዋል፡፡ የአካባቢው የዓይን ምስክሮችም ተጧሪ አረጋዊያንና ህፃናት “ውሃ፣ አምባሻ እያሉ በየመንገዱ ሲለምኑ ያለርህራሄ እየደበደቧቸው ወስደዋቸዋል፡፡” ሲሉ በቅሬታ ያስረዱሉ፡፡

የመንግስትን ዘር ማፅዳት ዘመቻ ማስቆም የሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃላፊነት ነው

ፍኖተ ነጻነት ርዕሰ አንቀጽ

አንባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት የጻፈው ግን የማያነበው፣ አስከብረዋለሁ የሚለው ግን የማያከብረው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገመንግስት በአንቀፅ 32 ማንኛውም ኢትዮጵያዊም ሆነ በህጋዊ መንገድ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖር የውጪ ዜጋ በነፃነት በመላ ሀገሪቱ የመንቀሳቀስ፣ የሚኖርበትን ቦታ የመምረጥ መብት እንዳለው ይደነግጋል፡፡

ለዜጎች መሞት፣ መፈናቀልና መሰደድ ተጠያቂው መንግስት ነው!!! ወንጀለኞች በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን!!

UDJ HeadPic21አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)
በተደጋጋሚ ፓርቲያችን እንደሚገልፀው አምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት የሚከተለው ቋንቋን መሰረት ያደረገ ፌደራሊዝምና የስርዓቱ አራማጆች ካላቸው የስልጣን እድሜን የማራዘም ጉጉት ተደማምረው ለሃገራችን እንዲሁም ተቻችሎ፣ ተዋልዶ፣ ተዛምዶና ተዋድዶ ለዘመናት ይኖር ለነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ ግልፅና አስፈሪ አደጋ ወደ መሆን እንደደረሱ በግላጭ እየታየ ነው፡፡

ታላላቅ የታሪክ ክህደቶች ከ“ፍኖተ ገድል”

ገብረመድህን አርአያ
ገብረመድህን አርአያ (ተጻፈ ሚያዝያ 6, 2004 ዓ.ም.)

ለአንድ ሰሞን ለአመታት በአሜሪካኗ ግዛት ኦሃዮ ውስጥ በስደት ሲኖር የነበረው የወያኔ ነባር ታጋይ፣ በስለላ የሰለጠነ … እና መሪህ ባኽታ ብስራት አማረ የጻፈው መጽሃፍ በህትመት ወጥቶ ጉድ፣ ጉድ ከተባለለት በኋላ እኔም እንደ ኢትዮጵያዊነቴ እና እንደ ቀድሞ የህወሃት ቀዳሚ ታጋይነቴ መጽሃፉን አግኝቼ ለማንበብ እና የግሌን ግምገማ ለማድረግ መፈለጌ አልቀረም። ዘግይቶም ቢሆን መጽሃፉ በእጄ ገብቶ የማንበብ እድል አገኘሁ። መቼም ጉድ ነው የሚባለው!! ህወሃት እና በዙሪያው የከበቡት ጉዶች የቅጥፈት እና የክህደት ጉድ ማለቂያ የለውም።

ይህ መጽሃፍ በተከታይ እትም ሊታረም የሚችል ግድፈት አይደለም የተሸከመው፤ እንደዚህ በአገጠጠ ውሸት፣ በህወሃታዊ የታሪክ ክህደት፣ በጥላቻ እና በተንኮል የታጨቀ መጽሃፍ አይቼም፣ አንብቤም አላውቅም። ብስራት አማረ ታሪክ ለዚያውም በጣም የቅርብ ጊዜ ታሪክ አንድ ሰው እንዳሻው ስለጻፈው የመጨረሻው እውነት ሆኖ ይቆያል ብሎ ያምናል። ይህ አስተሳሰብ ላዩን ሲያዩት በጣም ገራገር ሊመስል ይችላል። ነገር ግን በጊዜ አስፈላጊው የእርምት እና የማጋለጥ እርምጃ  ካለተወሰደ የኋላ ኋላ ብዙሃን እንደ  እውነተኛ ታሪክ እና ትንታኔ  ዋጋ ሰጥተው ሊያዩት ይችሉ ይሆናል።