Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Thursday, November 8, 2012

ኢህአዴግ ስንት ቦታ ሊሰነጠቅ ይችላል?

 በተመስገን ደሳለኝ
ብርዱ የጥቅምት ነው፤ አጥንት ድረስ ዘልቆ የሚያንቀጠቅጥ ኃይለኛ ቅዝቃዜ፡፡ አዲስ አበባ ገና ከእንቅልፏ በመንቃት ላይ ነች፡፡ ለስራ የቸኮሉ መንገደኞች ትራንስፖርት ፍለጋ ወዲያ ወዲህ ይካለባሉ፡፡ ማክሰኞ ጥቅምት 7 ቀን 2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ 12 ሰዓት ከ50 ደቂቃ ላይ ብስራተ ገብርኤል አደባባይ ‹‹መገናኛ ራዲዮ›› በያዙ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡

 የትራፊክ ፖሊሶቹ ስራ የበዛባቸው ይመስላሉ፡፡ 12 ሰዓት ከ55 ደቂቃ ሲል በሁለት የሞተር ብስክሌት በተፈናጠጡ የትራፊክ ፖሊሶች ፊት አውራሪነት አንዲት ሳይረን የተገጠመላት የፖሊስ ታርጋ የለጠፈች መኪና የ‹‹መንገድ ልቀቁልኝ›› ጩኸቷን እያንባረቀች አቋርጣ በማለፍ ወደ ሳር ቤት አቅጣጫ ከነፈች፡፡ ሶስት ‹‹ቪኤት›› መኪና ሰለሱ፡፡

Tuesday, November 6, 2012

የኦህዴድ ክፍፍል ወደ ዞን ባለስልጣናትም ወረደ

ኢሳት ዜና:-
OPDO
የኦህዴድ ክፍፍል ወደ ዞኖች ወርዷል፣ ይህን መንግስት ተቀብለን እንቀጥላለን ወይም አንቀጥልም የሚሉ ሁለት ቡድኖች መፈጠራቸውን አባላቱ ገለጡ ስማቸው እንዳይገለጥ ያስጠነቀቁ የኦህዴድ ባለስልጣናት ለኢሳት እንደገለጡት በኦህዴድ ከፍተኛ አመራሮች የተፈጠረው መከፋፈል ወደ ዞኖች ወርዶ በድርጅቱ ውስጥ ሁለት ቡድኖች እንዲፈጠሩ አድርጓል።

ከፍተኛ ክፍፍል በሚታይበት በሀረሪ ክልል ፣  በአንድ በኩል ይህንን ስርአት ደግፈን መጓዝ አለብን የሚሉ  ኦህዴዶች ደጋፊዎችን ለማሰባሰብ ሙከራ በማድረግ ላይ ሲሆኑ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ” ብዙሀን እንዴት በአናሳ ቡድን ይገዛሉ? ” በማለት ስርአቱን አንቀበልም ያሉ ሀይሎች የራሳቸውን ደጋፊ በማሰባሰብ ቡድን እየፈጠሩ ነው።

በሲዳማ ዞን ቡና አምራች አርሶ አደሮች ተቃውሞ አስነሱ

ኢሳት ዜና:-በደቡብ ክልል፣ ሲዳማ ዞን፣ በንታ ወረዳ ቡና አምራች ገበሬዎች ተቃውሞውን ያነሱት የቡና መሸጫ ዋጋ ከወቅቱ የገበያ ዋጋ ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ ሆኖአል በማለት ነው።

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የይግባኝ ወረቀቱን በእስር ቤት ሀላፊዎች ተነጠቀ

Journalist Eskinder Nega
ኢሳት ዜና:-በሽብር ወንጀል ተከሶ 18 ዓመታት የግፍ እስር የተፈረደበት ታዋቂው  ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ዛሬ ረፋዱ ላይ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ለማቅረብ ተገኝቶ ነበር። እስክንድር  ይግባኝ ለማለት ዝግጅቱን ያጠናቀቀ ቢሆንም፣ የይግባኙን ሰነድና ለፍርድ ቤት ሊያቀርበው ያዘጋጀውን የወረቀት ማስታወሺያዎች የቃሊቲ እስር ቤት ፖሊሶች ስለነጠቁት ሳይችል ቀርቷል።

ጋዜጠኛ እስክንድር ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ለእስር ቤት ፖሊሶች ትእዛዝ እንዲጻፍለትና አጭር ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል።

Sunday, November 4, 2012

ከአሥር ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከኢትዮጵያ 15 ቢሊዮን ዶላር መውጣቱ ተረጋገጠ, ካቻምና ብቻ 3.5 ቢሊዮን ዶላር ታጥቷል: በአስራት ሥዩም


 እ.ኤ.አ. ከ2001 እስከ 2010 ባለው ጊዜ ውስጥ 15 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገንዘብ ሕጋዊ በሆነና ባልሆነ መንገድ ከኢትዮጵያ እንዲወጣ ተደርጎ ወደ ውጭ ገበያዎች ማምራቱን በቅርቡ ይፋ የሆነ ሪፖርት አመለከተ፡፡ ይህ ችግር በመላ አፍሪካ ትኩረት እየሳበ እንደመጣ ታውቋል፡፡

የፋይናንስ ምንጭ በእጅጉ ከሚያስፈልጉዋቸው ታዳጊ አገሮች ወደ ሌሎች አገሮች ገንዘብን በማዘዋወርና በሕገወጥ የፋይናንስ ግብይት እየወጣ ያለውን ሀብት በተመለከተ እ.ኤ.አ. ከ2009 ጀምሮ ሲወጡ የነበሩ ሪፖርቶች የሚያረጋግጡት፣ ክስተቱ ትኩረት እየሳበ መምጣቱን ነው፡፡ ኢትዮጵያ ያላትን ውስን የውጭ ምንዛሪ መጠን ይኼው ከፍተኛ የካፒታል ማዛወር ወይም ማሸሽ ተግባር በእጅጉ እየታየባት በመምጣቱ፣ የመነጋገርያ አጀንዳ እንድትሆን አድርጓታል፡፡

በመከላከያ የጀኔራሎች ፍጥጫ

M.general Molla H.Mariam
(እየሩሳሌም አርአያ)
በመከላከያ ያለው ሽኩቻ እየበረታ ሄዶዋል። በጄ/ል ሳሞራ ትዕዛዝ የአየር ሓይል አዛዥ የነበሩት ጄ/ል ሞላ ሃ/ማሪያም ከሃላፊነት እንዲነሱ ተደርጎዋል። በምትካቸው ደግሞ ጄ/ል መሃሪ ዘውዴ እንደሚቀመጡ ታውቓል። በቅርቡ የሜ/ጄኔራልነት ሹመት ያገኙት እና ወዲ ዘውዴ በሚል የሚጠሩት ጄ/ል መሃሪ ዘውዴ ከበረሃ አንስቶ ከሳሞራ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት እንዳላቸው ከዚህ ቀደም ጠቁሜ ነበር። የሹመታቸው ምስጢሩ ሳሞራ ናቸው። ካኤርትራ የሚወለዱት ወዲ ዘውዴ ከሳሞራ ባለፈ ለመለስ ታማኝ አገልጋይ የነበሩ ናችው። በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት « ፈሪ» ተብለው እንደተገመገሙ ታማኝ ምንጮች አስታውሰዋል።