Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Saturday, August 4, 2012

ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ በኩዌት ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ እራሷን አጠፋች

ኢሳት ዜና:- ሐምሌ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
አረብ ታይምስ ትናንት ባወጣው ዘገባ እንደገለፀው ከሆነ፣ ኢትዮጵያዊቷ ትሰራበት የነበረው ቤት ውስጥ ራሷን የመግደል ሙከራ ስታደርግ ተይዛ ወደ ሆስፒታል ተወስዳ ስነልቦና ሕክምና እንድትወስድ ተደርጋ ነበር።

ሆኖም ከሆስፒታሉ ስትወጣ  “ጃሃራ” በሚባል ስፍራ ወደሚገኘው “አል-ነኢም” ፖሊስ ጣቢያ ተወስዳ በመታሰር በምርመራ ላይ ሳለች፤ የእስር ቤቱ መታጠቢያ ቤት ውስጥ አድርጋው በነበረው ሂጃብ  የራሷን ሕይወት አጥፍታ ተረኛው ፖሊስ እስረኞችን በሚጎበኝበት ወቅት አስከሬኗን ማግኘቱን ዘግቧል።

አረብ ታይምስ ሟቿ ኢትዮጵያዊ መሆኗን ከመግለጽ በቀር ስለማንነቷ የገለፀው ምንም አይነት መረጃ የለም።

ሚኒስትሩ አቶ ጁነዲን ሳዶ ይቅርታ አልጠይቅም አሉ

ኢሳት ዜና:- ሐምሌ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ባለቤታቸው የታሰሩባቸው የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትሩ አቶ ጁነዲን ሳዶ፦”ይቅርታ ጠይቁ” በመባላቸውን በመጥቀስ፦” የሠራሁት ስህተት ስለሌለ የምጠይቀው ይቅርታ የለም” አሉ። ባለቤቴ  ከህፃናት ልጆች ተነጥላ ትክክለኛ ባልሆነ ማስረጃ ታስራብኛለች ሲሉም  አቤት አሉ።

ሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ  የባለቤታቸውን መታሰር አስመልክቶ በኢትዮ ቻነል እና በሰንደቅ ጋዜጦች ለወጡት ዜናዎች መልስ በሰጡበትና በዛሬው የ ኢትዮ ቻነል ጋዜጣ ላይ በታተመው ጽሁፋቸው  ፤በጋዜጦቹ የወጡትን ጽሁፎች ተከትሎ  ባለቤታቸው  ከሰሞኑ የ እስልምና ተከታዮች እንቅስቃሴ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው ተደርጎ የሚወራው ስህተት እንደሆነ ገልጸዋል።

በደቡብ ክልል በፕሬዚዳንቱና በአፈ ጉባኤዋ መካከል በተፈጠረው ውዝግብ ምክር ቤቱ ለሁለት ተከፈለ

ኢሳት ዜና:- ሐምሌ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ባለፈው ማክሰኞ የክልሉ ፕሬዚዳንት የሆኑት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ከሲዳማ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች የተውጣጡ የአገር ሽማግሌዎችን ሰብስበው “የሲዳማ ጥያቄ ፣ ወቅታዊ አለመሆኑንና አብዛኛውን ህዝብ የማይወክል መሆኑን” ተናገሩ በማለት ለማግባባት ሞክረው እንደከሸፈባቸው መዘገባችን ይታወሳል።

ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ከሌሎች የመገናኛ ብዙሀን የተወከሉ ጋዜጠኞች በስፍራው ተገኝተው “የሲዳማ ጥያቄ  የጸረ ሰላም ሀይሎች ጥያቄ ነው” በማለት ይዘግባሉ ተብሎ ሲጠበቅ፣ ስብሰባው በውዝግብ ተደምድሟል።

የአቶ መለስ ዜናዊ መጨረሻ አሁንም የኢትዮጵያውያን ያልተመለሰ ጥያቄ ሆኗል

ኢሳት ዜና:- ሐምሌ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
እጅግ ውስብስብ የሆኑ ሚስጢሮችን በማውጣት የሚታወቁት አለማቀፍ የመገናኛ ብዙሀን የአቶ መለስን የደህንነት ሁኔታ ለማወቅ አለመቻላቸው ብዙዎችን አነጋግሯል። አንዳንድ ወገኖች የምእራባዊያን የመገናኛ ብዙሀን ከአሜሪካ ወይም ከአውሮፓ መንግስታት የ”ይለፍ መብራት” ካልበራላቸው፣ ዜናዎችን ለማውጣት ፈቃደኛ አይሆኑም በማለት ሲናገሩ ሌሎች ደግሞ ኢትዮጵያ የምእራባዊያን የመገናኛ ብዙሀን የምትስብ አገር ባለመሆኑዋ የመገናኛ ብዙሀኑ ትኩረት እንደነፈጉዋት ይገልጣሉ።

በመሀሉ በርካታ ኢትዮጵያውያን ወደ ተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን ድረገጾች በመግባት ዜናዎችን በእየለቱ ይቃርማሉ። አንዳንድ ኢትዮጵያውያን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጣን ቦታ መራቅ ለኢትዮጵያ አዲስ ተስፋን ይዞ ሊመጣ ይችላል ሲሉ፣ ሌሎች ወገኖች ደግሞ፣ በፍትህ ጋዜጣ ላይ የደረሰውን በመፍራት ከእስካሁኑም የባሰ አፋኝ መንግስት እንዳይመጣ ይሰጋሉ።

የሱዳን የደህነት አባላት የቤንሻንጉል ነጻ አውጭ ድርጅትን መሪ ልጅ አሰሩ

ኢሳት ዜና:- ሐምሌ ፳፯ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
መንግስት ሰሞኑን ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ነጻ አውጭ ድርጅት ሰራዊት አባላት ጋር ድርድር በማድረግ ስምምነት ላይ መድረሱን አስታውቆ ነበር።

የኢትዮ ቻነል እና የሳምሶን ማስታወቂያ ድርጅት ባለቤት የሆነው ሳምሶን ማሞ ከነ ባለቤቱ ታሰረ

ኢሳት ዜና:- ሐምሌ ፳፯ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
የኢትዮ-ቻናል ጋዜጣ ማኔጂንግ ዳይሬክተርና የሳምሶን አድቨርታይዚንግ ዋና ስራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ሳምሶን ማሞ እና የኢትዮ-ቻናል ጋዜጣ አሳታሚ የዜድ ፕሬስ ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ዘውድነሽ ታደሰ ባለፈው ሐሙስ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል ::

በጋምቤላ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነርና ሌሎች 4 ባለስልጣናት ያለመከሰስ መብታቸው ተነሳ

ኢሳት ዜና:- ሐምሌ ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ባለፉት ሁለት ወራት በጋምቤላ ክልል ነዋሪዎች እንዲሁም የሼክ ሙሀመድ ሁሴን አላሙዲን ኩባንያ ሰራተኞች ላይ በተፈጸመው ጥቃት ፣ ከታጣቂዎች ጋር በመሆን ጥቃቱን አስፈጽመዋል የተባሉት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር ያለመከሰስ መብታቸው በክልሉ ምክር ቤት እንዲነሳ ተደርጓል።

Friday, August 3, 2012

ሀገሪቱ በማን እየተመራች ነው?, በብስራት ወ/ሚካኤል

ሰው ከዚህች ዓለም ፍጡር አንዱ ብቻ ሳይሆን መኖሪያቸውን በምድር ያደረጉትንም እንዲገዛና እንዲጠቀም የተፈቀደለትም ጭምር ፍጡር ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን እንደሚዋለድ እንደሚያድግ እና እንደሚሞት መረሳት የለበትም፤የሰው ልጅ ሟች ነውና፡፡

እንዳለመታደል ሆኖ የገዥው ቡድን መሪዎች ግን ብዙዎች ተሰውተው እዚህ የደረሱ መሆናቸው እንኳ ያሰቡት አሊያም የሚያስቡት አይመስልም፡፡እነኚህ ሰዎች ደግሞ ከታሪክና ትውልድ ሳይሆን ከአደጋ እንጂ ከሌላ መማርን የሚፈቅዱ መስልም፡፡ 

የአማራ ክልል ወጣቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ከአገር ተሰደደ

ኢሳት ዜና:- ሐምሌ ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
የአማራ ክልል የወጣቶች ማህበር ፕሬዚዳንት በመሆን ያገለገለው፣ በክልሉ ውስጥ በወጣቱ ዘንድ ከፍተኛ ከበሬታ ያተረፈውና ወጣቱን ለለውጥ ለማንቀሳቀስ ከፍተኛ ስራ መስራቱ የሚነገርለት ወጣት ዘመነ ካሴ እንዲሁም የህግ ምሩቃን የመሰረቱት የአባይ ፍሬዎች ወጣቶች ማህበር ሊቀመንበር የሆነው ከፍያለው ጌጡ ከገዢው ፓርቲ የደህንነት ሰዎች ክትትል አምልጠው ወደ ሶስተኛ አገር ተሰደዋል።

ከመለስ አስተዳደር በኋላ የሚጠበቁ ክስተቶች, በፕሮፌሰር መሳይ ከበደ


የፈላጭ ቆራጭ አምባገነናዊ ስርዓት እና በአንድ ግለሰብ ላይ የተከማቸ ስልጣን ዋንኛው ችግር፤ ቋማዊ የስልጣን ሽግግርን ሊያስተገብር አለማስቻሉ ነው፡፡ በአብዛኛው እንዲህ ያሉ የስልጣን ሽግግር መንገዶች በተጻፉ እና ዋጋ ባላቸው ሕገ መንግስቶች ውስጥ ተካተው ይገኛሉ፡፡ 

ቢሆንም ቅሉ ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ እና ኃይልን በማንአለብኝነት የመጠቀም አካሄድ ከጥቅም ውጪ አድርጎ ለሚንዳቸው፣ ተቋማት ቅቡልነትንም ሆነ ህዝባዊ ከበሬታን ሊያተርፉ አይችሉም፡፡ ይልቁኑም ስልጣንን የማስተላለፍ ግድ-ባይነት በተለያዩ ተቀናቃኞች መሀል መራር ሽኩቻን ይቀሰቅሳል፡፡ የተቀናቃኞች እንደአሸን መፍላት፣ ሀይልን በማንአለብኝነት የመጠቀም ተፈጥሯዊ ውጤት ነው፡፡ ስልጣን/ ኃይል ከቅቡልነት ማዕቀፍ ውጪ ሲተገበር፤ ለስልጣን ተፎካካሪዎች የሚያስተላልፈው መልእክት ተነጥቆ መወሰድ ያለበት ነገር መሆኑን ነው፡፡ ይህም የተቀናቃኞችን ሽኩቻ ያንረዋል፡፡ ሌላው የፈላጭ ቆራጭ ኃይል መልፈስፈስ የሚያስከትለው ውጤት ለህዝባዊ አመጽ የመነቃቃት አዝማሚያን ነው፡፡ 

በሞያሌ ከተማ ውስጥ ውጊያ ተካሄደ

 -ሞያሌ የሚገኘው የጦር ካምፕ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል
ከኬኒያ ጋር በድንበር ከተማነትና በደረቅ ወደብነት በማገልገል ላይ በምትገኘውና በኦሮሚያና በሱማሌ ክልላዊ መንግስት በጋራ በምትተዳደረው ሞያሌ ከተማ ሐምሌ 20 ቀን 2004 ዓ.ም ውጊያ መከናወኑን ከሥፍራው ምንጮቻችን ገለፁ፡፡ ምንጮቻችን እንደሚሉት የአደጋውን መጠን በትክክል ለመግለጽ ቢቸገሩም ከ20 በላይ የሰው ህይወት መጥፋቱን እና በህይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደነበር አስታውቀዋል ፡፡

Wednesday, August 1, 2012

በረከት ስምኦን “መለስ አልሞተም” አለ! ሙክታር ከድር የመለስን ቦታ ሸፍኖ እየሰራ መሆኑ ታወቀ!!

ኢ.ኤም.ኤፍ (ልዩ ዘገባ) – በአሁኑ ወቅት የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ከህክምና አገግሞ ለስራ ባለመብቃቱ፤ በሬዲዮ ፋና በኩል… “ጠቅላይ ሚንስትሩ ከሞተ ማን ተክቶ ይሰራል?” በሚል ርዕስ ሰፊ ውይይት ተደርጎ ነበር።

 በዚህም ውይይት ወቅት የህግ ሰዎች “በምትኩ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ ኃይለማርያም ደሳለኝ ተክቶት ይሰራል” የሚል ትንታኔ ሰጥተዋል። ይህ እንግዲህ በኢህአዴግ ሬዲዮ ፋና በኩል የተደመጠ ነው። በተግባር ግን አሁን የጠቅላይ ሚንስትሩን ቢሮ ስራ እየሰራ የሚገኘው የቀድሞው የኦሮሚያ ምክትል ፕሬዘዳንት የነበረው፣ ሙክታር ከድር መሆኑ ታውቋል። 

በአሜሪካ ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶችን እና ማኅበራትን የሚቃወም ድብቅ የካህናት ስብሰባ እየተካሄደ ነው

(ደጀ ሰላም፤ ሐምሌ 25/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 1/ 2012)፦ በሰሜን አሜሪካ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ከርስቲያን በምዕራብ ስቴቶች የካሊፎርንያ ሀገረ ስብከት ሥር በሚተዳደሩ አቢያተ ክርስቲያናት ውስጥ የሚያገለግሉ ጥቂት ካህናት፤ ማኅበረ ቅዱሳንን፤ ማኅበረ በዓለ ወልድንና የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤንና በጠቅላላው ለቤተ ክርስቲያናቸው የሚቀኑ ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶችን እና ካህናትን የሚቃወም ድብቅ ስብሰባ እየተካሔደ ነው። 
የመድረክ አባል ድርጅቶች የሆኑ፣ የኦሮሞ ሕዝብ ኮንግረስ እና የኦሮሞ ፌደራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ በብዙዎች ሲጠበቅ የነበረዉን የፓርቲዎቻቸዉን ዉህደት፣ አመራሮቻቸዉ ባደረጉት ስብሰባ አጸደቁ።

የውጭ ጉዳይ ዜናዎች

 Source:ecadforum news
በሙሉነህ ዮሃንስና የውጭ ጉዳይ ምንጮች የተጠናከረ (ጁላይ 31 2012)
  • አምባሳደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ መለስን ሲያስታምም ከርሞ ከብራስልስ ወደ አዲስ አበባ እየተመለሰ ነው!
  • አምባሳደር ሙሉጌታ አለምሰገድ ባጣዳፊ ቤተሰቡን ወደ ጣሊያን አሸሸ!
  • አሜሪካን ሃገር በአምባሳደርነት ማእረግ ያሉ አራት ዲፕሎማቶች ከአበበ ገላው ጋር በተያያዘ ጠቅልለው እንዲመለሱ ታዘዙ!
  • መጠኑ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብና የባለስልጣናት ቤተሰቦች ወደ ኬንያ እየተሸጋገሩ ነው!
አምባሳደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ መለስን ሲያስታምም ከርሞ ከብራስልስ ወደ አዲስ አበባ እየተመለሰ ነው!

Tuesday, July 31, 2012

ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሕመም የዋልድባ መነኰሳት ተጠያቂ ተደረጉ


  • ከአብረንታንት እና ማይ ለበጣ ሁለት መነኰሳት ወደ ማይ ፀብሪ ተወስደዋልበዶንዶሮቃ 50 በላይ የመነኰሳት እና መነኰሳዪያት ቤት በፖሊስ ተፈትሿል
  • ከፖሊሶቹ አንዲቱ ከጾታዋ የተነሣ ወደ ዋልድባ ለመግባት የማይፈቀድላት ሴት ናት
  • የአብረንታንቱ አባ ገብረ ሥላሴ ዋለልኝ እንደታሰሩ ናቸው
  • 49 ያላነሱ የቤተ ሚናስ መነኰሳት በፖሊስ ይፈለጋሉ
  • ‹‹እናንት ምታታሞች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ መታመም ተጠያቂዎች ናችሁ›› /የማይ ፀብሪ ፖሊሶች/

Monday, July 30, 2012

የህወሃት አባላት ስብሰባ እንዲጠራ እየጠየቁ ነው!

ልዩ ግምገማ)
ኢ.ኤም.ኤፍ – ከቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ድንገተኛ ህመም በኋላ ከህወሃት አካባቢ መልካም ወሬ አይሰማም። በውጭ ሲታይ አሁንም የጠነከሩ ቢመስሉም ውስጥ ውስጡን ግን መጎሻሸማቸው አልቀረም። በተለይም የህወሃት (ህዝባዊ ወያነ ሃርነት ትግራይ) ሊቀ መንበር የነበረው መለስ ዜናዊ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ተሽሎት ወደ ስራ እንደማይመለስ በመገለጹ፤ ከሌሎች የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ይልቅ የህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት አስቸኳይ ስብሰባ እንዲጠራላቸው ለጽ/ቤቱ ጥያቄ ቢያቀርቡም ምንም ምላሽ እንዳልተሰጣቸው ለማወቅ ተችሏል። 

Sunday, July 29, 2012

VOA: Prof. Alemayehu G Mariam on Meles Zenawi and Power Succession Rights

Constitution guarantees no right for power succession: prof. Al Mariam

Professor Alemayehu Gebre Mariam tells Tizita Belachew of VOA that the Ethiopian consitution doesn't guarantee the transfer of power in the event of the death of the prime minister. He said in fact the deputy prime minister, who is expected to automatically replace the deceased pm, is only accountable to the PM, and doesn't have any clearcut succession rights.

የወያኔዎች አይረሴ አባባሎች (Highlights)

በተሻለ መንግሥቱ

1. “ኤርትራ ከየት ወዴት” –
የኢትዮጵያዊው መለስ ዜናዊ መጽሐፍ ፡፡ ስለ‹እናት ሀገሩ› ኢትዮጵያ አንድም አንቀጽ አለመጻፉን ልብ ይሏል፡፡
2. “በእናንተ ወገብ ላይ ያለው ቁስል በእኔም ወገብ ላይ አለ፡፡” መለስ ዜናዊ እነ ንጉሤ አስገልጠውን የመሰሉ ሆዳም አማሮችን አሥመራ ላይ አስጎንብሶ ሻዕቢያን ይቅርታ ባስጠየቀበት ዘመን በትግርኛ ተናግሮት ወዳማርኛ ከተመለሰው፡፡
3. “የአማራ ተረትና የሶማሌ በጀት ነው ያስቸገረን፡፡” መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት የተናገረው፡፡