Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Saturday, May 26, 2012

ልምሰል የሞላለት

















ልምሰል የሞላለት
አዎ "ልምሰል የሞላለት ! "
በልቸ ጠጥቸ ስለኖርኩ በድሎት i
መብቴ ተገፎ አጥቼ ነጻነት
በስደት ሃበሳ ስኖር ስንከራተት፤
የደላኝ ይመስላል ! አኗኗሬን ሲቃኙት፤
የደላኝ ይመስላል ! ተክለ ቁመናየን መላብሴን ሲያዩት፤
የደላኝ ይመስላል! ስናገር ሲያደምጡኝ የምኖር በስኬት !
ታዲያሳ. . . !
በአደባባይ ልሳቅ ከቶ ምን አለበት
በደስታ ልምነሽነሽ ልምሰል የሞላለት
ኑሮ ግብግቡን አስተውለው ሲያዩት፤
ድብብቆሽ ኑሮ፤ አለፋውን ስቅየት
የመንገዱን ርቀት የሰው ልጅን ክፋት፤
ሲታዘቡት ውለው ሲያሰላስሉ ቢያድሩት፤
ምስለኔያችን ከፍቶ ሲደሰኩት ኩሸት፤
ሰብዕና ጠፍቶ ሰው ሁሉ ሲራኮት፤
ወገኔ ዝም ብሏል ቤቱ እስኪደርስበት፤
ደፋር ይናገራል እሱ ምናለበት
"
እድል እጣቸው ነው የተፈጠሩበት"
"
ለምን መጡ" ይላል መድገፉ ጠፍቶት፤
ይለናል ጎረምሳው መደገፉ ጠፍቶት
ድምጽ ማሰማቱ ፤ውሃ ማቅረብ ገዶት
እናም. . .
ስላየሁ በአይኖቸ ይህን መሳይ ትንግርት፤
ስላየሁ ህይዎቱን የዳፋ ቀማሹ የመሪሩን ስደት፤
ያስታግሰው እንደሁ የንዳድ ቃጠሎ የብሽቀቴን ብርታት፤
ድብቅ ሽሽግ ብየ . . .ሲለኝ አለቅሳለሁ ለመረረው ህይዎት፤
አዎእውነት ብለሃል ወንድም አደም
ይህ ነው የእውነቱ ገጽታ የዚህች አለም . . .
"
በጨለውማ ተስፋ ፤ጥርሴ ጧፍ ከሆነ
የህይዎቴን ግርዶሽ ገላልጦት ካደረ፤
ምናለ ልሳቀው ባንች ሆየ ቅኝት
ልንከትከት በዜማ ልምሰል የሞላለት !"
                     ©  ©  ©
        ወዳጀ አደም ሁሴን ዘራፍ አስባልከኝ እኮ ) ! ግጥም ደስ ይላል . . . የላክልኝ ግጥም ውስጤን ነካችውና ከተጋደምኩበት ይህችኑ ቋጠርኩልህ ! ስንኝ መገጣጠሙን በትክክል አሳክቸዋለሁ ባልልም ስሜቴን ካስረዳልኝ ይበቃል! ገጣሚ አይደለሁ እንዳንተ ! ለሁሉም ይህችም ላንተ ትሆን ዘንድ ፈቅጃለሁ !
ነቢዩ ሲራክ

አምነስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት መቀጠሉን ገለጠ

ኢሳት ዜና:-
አለማቀፉ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት ፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው የ2012 አዲስ ሪፖርት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸሙትን የሰብአዊ መብት ረገጣዎች በዝርዝር አቅርቧል። 

በአረቡ አለም የታየውን ህዝባዊ አመጽ ተከትሎ የመለስ መንግስት አምና በመጋቢት እና በሚያዚያ ወራት 250 የኦሮሞ ፌደራሊስት ዲሞክራቲክ ንቅናቄ እና የኦሮሞ ህዝብ ኮንግረስ አባላት መታሰራቸውን፣ በሰኔ ወር ደግሞ ውብሸት ታየ፣ ርእዮት አለሙመ ዘሪሁን ገብረእግዚአብሄርና ደጄኔ ተፈራ መታሰራቸውን ገልጧል።

በሀምሌ ወር የስዊድን ጋዜጠኞች ማርቲን ሽብየና ጆሀን ፔርሰን ፣ በነሀሴና መስከረም ደግሞ በቀለ ገርባና ኦልባና ሊሌሳ ፣ አንዱአለም አራጌ፣ እስክንድር ነጋና ሌሎችም መታሰራቸውን ገልጠዋል።  በህዳር ወር 107 የተቃዋሚ ደርጅቶች መሪዎችና ጋዜጠኞች በሽብርተኝነት መከሰሳቸውን እንዲሁም አልጀዚራ፣ የአሜሪካ ድምጽ፣ ኢሳት ቴሌቪዥን፣ አዲስ ነገርና አምነስቲ ኢንተርናሽናል ዌብሳይት መታፈናቸውን ድርጅቱ ገልጧል።

በእስር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞችና የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች በእስር ቤት ውስጥ አሰቃቂ ድብደባ እና እንግልት በዝርዝር አብራርቷል። በደቡብ፣ በጋምቤላ፣ በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በሶማሊያ፣ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውን ያለፍላጎታቸው መፈናቀላቸውን አትቷል።

አምነስቲ በዚህ አመት ሪፖርቱ የምእራባዊያን መንግስታትን ክፉኛ ወቅሷል፡፡ የምእራባዊያን መንግስታት   በተለያዩ አገራት ሰብአዊ መብቶች ሲጣሱ አይተው እንዳላዩ ሆነው ማለፋቸው የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እንዲጨምር እንዳደረገው ጠቅሷል።

በአዲስ አበባ አትክልት ተራ ፤ፖሊሶች ከነጋዴዎች እና ከነዋሪዎች ጋር ተጋጩ

ኢሳት ዜና:-
ትናንት ፣ መጋቢት 16፣ 2004ዓም በአትክልት ተራ ፖሊሶች አንድ አትክልት ሻጭን መደብደባቸውን ተከትሎ፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ተቃውሞ በማሰማቸው ፖሊሶች ወደ ሀይል እርምጃ አምርተዋል።

በተከራይ እና አከራይ  መካከል የተነሳን ውዝግብ ሳቢያ  በጉሊት ሽያጭ የሚተዳደር ሰኢድ ኡመካ የተባለ ወጣት በፖሊሶች በመደብደቡ፤ የአፍሪካ አንድነት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተቃውሞአቸውን በጩኸት አሰምተዋል። 

ጩኸቱ ወደተካረረ ፍጥጫ አምርቶ ግጭት ማስከተሉን የገለጹት የዜናው ምንጮች፤ ነዋሪዎች ከፖሊሶች ጋር በፈጠሩት በዚሁ ግብግብ ፖሊሶችን ጨምሮ የአካባቢው ነጋዴዎች እና ሸማቾች ጉዳት እንደደረሰባቸው እና ከ15 ያላነሱ ሰዎችም ለእስር እንደተዳረጉ አመልክተዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በመርካቶ በንግድ ሥራ ውስጥ ከተሰማሩት ወገኖች መካከል 75 በመቶ ያህሉ ሕገወጥ ናቸው በሚል አዲስ ዘመቻ ለመክፈት መዘጋጀቱን ምንጮች ጠቆሙ፡፡ ባለሥልጣኑ በጥናት ደርሼበታለሁ ባለው መሰረት በመርካቶ ሕጋዊ ንግድ ፈቃድ አውጥተው የሚሰሩ ነጋዴዎች ቁጥር 25 በመቶ ብቻ ሲሆኑ የተቀሩት 75 በመቶ ያህሉ ንግድ ፈቃድ የሌላቸውና ግብርም የማይከፍሉ ናቸው ብሏል፡፡

ጥናቱ አያይዞም በሃገሪቱ ካለው አጠቃላይ የገንዘብ ልውውጥ ግማሸ ያህሉን የሚይዘው የመርካቶ አካባቢ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ ከዚሁ ጥናት ጋር በተያያዘም ባለሥልጣኑ “የመርካቶ ፕሮጀክት” በሚል በመርካቶ አካባቢ ሁለት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እና አሰር የታክስ ማዕከላትን ከፍቷል፡፡

በጉዳዩ ላይ አስተያየት የተጠየቁ አንድ በመርካቶ አካባቢ በንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴ እንደተናገሩት በአካባቢው ንግድ ፈቃድ አላወጡም የሚባሉት መንገድ ላይ ከፖሊስ ጋር ግብግብ ገጥመው የእለት ግርሳቸውን የሚሸፍኑ አነስተኛና ጥቃቅን ነጋዴዎች ሁሉ ተቆጥረው መሆኑን አስታውሰው እነዚህ ወገኖች ግብር ክፈሉ ብሎ ማሳደድ ደሃው ሕዝብ ትንሸ ነገር ሰርቶ እንኳን እንዳያድር ከማድረግ ያለፈ ፋይዳ የለውም በማለት የባለስልጣኑን እርምጃ ተቃውመዋል፡፡

ባለሥልጣኑ ባለፈው ዓመት ከ51 ቢሊየን ብር በላይ ግብር መሰብሰብ የቻለ ሲሆን ዘንድሮ 76 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ቢያቅድም ባለፉት አስር ወራት ብቻ መሰብሰብ የቻለው 59 ቢሊየን ብር ገደማ መሆኑ ጋር ሲነጻጸር በቀሪ ሁለት ወራት ዕቅዱን የማሳካቱ ነገር ጥያቄ ምልክት ውስጥ ያለ ነው፡፡የመርካቶ ፕሮጀክት የባለሥልጣኑን እጅግ የተጋነነ የገቢ ዕቅድ ለማሳካት ሊጠቅመው ይችላል ተብሏል::

ባለሥልጣነ  አምና በደረጃ “ሐ” ሥር ያሉ አነስተኛ ነጋዴዎችን በተመለከተ አጠናሁት ባለው ጥናት መሰረት ደረጃቸውን በድንገት በማሳደጉ አነስተኛና ጥቃቅን ንግድ ላይ የተሰማሩ ወገኖች ጭምር በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ግብር እንዲከፍሉ መጠየቃቸው ከፍተኛ ተቃውሞን ቀስቅሶበት እንደነበር ያታወሳል፡፡

በተጨማሪም አምስት ሺ ብር የማይሞላ ካፒታል ያላቸው ወገኖች ጭምር ካሸ ሬጅስተር የተባለውን ማሸን ከብር ስምንት ሺ በላይ አውጥተው እንዲገዙ መጠየቃቸውም እንዲሁ ተመሳሳይ ተቃውሞን አስነስቶበት ነበር፡፡ባለሥልጣኑ ገቢን ለማሳደግ ብቻ የያዘው ሩጫ ከበርካታ ነጋዴዎች ጋር እያላተመው እንደሚገኝም ይታወቃል፡፡

Friday, May 25, 2012

VOA Reporter Detained in Ethiopia

A Voice of America reporter has been detained in the Ethiopian capital while trying to cover a demonstration Friday. Witnesses to the arrest said that reporter Peter Heinlein and his translator Simegineh Yekoye were detained while seeking to interview protesters during a Muslim demonstration following Friday prayers in Addis Ababa.
Another Western reporter said there was a heavy police presence at the demonstration and that he also was stopped by police and told to leave the area. 
Tom Rhodes, East Africa spokesman for the Committee to Protect Journalists (CPJ), said he understood that Heinlein was accused of acting "unprofessionally and illegally." Rhodes said a government spokesman accused Heinlein, who is married to a Danish diplomat, of improperly using a diplomatic vehicle and refusing to show media accreditation.

Rhodes added that the accusations seemed at odds with Heinlein's reputation as a highly professional journalist who has worked for VOA since 1988."However, I would add that Peter Heinlein is a veteran reporter, an experienced and professional broadcaster, so personally I find it rather hard to believe that someone like Heinlein would be reporting unprofessionally," Rhodes said.

In a formal statement from its headquarters in Washington, VOA said, "The safety and welfare of our reporters is our utmost concern and we are working to gather more information about Mr. Heinlein’s status." The statement said VOA is in touch with the U.S. Department of State seeking more information and that it is urging "Ethiopian authorities to allow Mr. Heinlein to carry out his journalistic responsibilities without interference.”
Heinlein reported last week on rising tensions between the government and Ethiopia's Muslim minority, which has held a series of demonstrations to protest what the community sees as government interference in Islamic affairs. The CPJ quoted Minister of Government Communications Bereket Simon saying officials wanted to speak to Heinlein about his "unobjective" reporting on the Muslim issue. Bereket did not say whether Heinlein has been formally arrested or charged.

Thursday, May 24, 2012

በጋምቤላና በቤንሻንጉል የፀጥታና የማስፈጸም ችግሮች ለፕሮጀክቶች እንቅፋት ሆነዋል

By Ethiopian Reporter
በአቶ አዲሱ ለገሰ የሚመራው የፌዴራል መንግሥት ልዑካን ቡድን በጋምቤላና በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልሎች ባካሄደው የመስክ ግምገማ፣ የመንደር ማሰባሰብ ሥራዎች ችግር እየገጠማቸው መሆኑን አረጋገጠ፡፡ 

አቶ አዲሱና የቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ፀጋዬ በርኸ የሚገኙበት የልዑካን ቡድን ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ድረስ በሁለቱ ክልሎች ስብሰባዎችንና የመስክ ጉብኝቶችን አካሂዶ ባለፈው እሑድ ተመልሷል፡፡

በዚህ ወቅት በቤንሻንጉል ክልል በዋናነት ፕሮጀክቶችን በማስፈጸም በኩል ደካማ የሥራ አፈጻጸም ሲያሳይ፣ በጋምቤላ ክልል ደግሞ ቀደም ሲል የተፈጠረው የፀጥታ መደፍረስ ፕሮጀክቶች የተፈለገውን ያህል መራመድ እንዳይቻሉ ማድረጉ ተጠቅሷል፡፡ የፌዴራል መንግሥት በ2004 ዓ.ም. የምዕተ ዓመቱን የልማት ግቦች እንዲሳኩ ለማድረግ ለሁሉም  ለክልሎች የሚከፋፈል 15 ቢሊዮን ብር መድቧል፡፡ 

የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ከዚህ ገንዘብ ውስጥ 294 ሚሊዮን ብር ሲደርሰው፣ በዚህ ገንዘብ በዋናነት ተበታትነው የሚገኙ የክልሉን ነዋሪዎች በመንደር ማሰባሰብ፣ ውኃ፣ ጤናና የትምህርት ተቋማትን የማሟላት ሥራ የመሥራት ዕቅድ ተይዟል፡፡ ነገር ግን የበጀት ዓመቱ ሊጠናቀቅ አንድ ወር ብቻ እየቀረው ክልሉ ከዚህ ገንዘብ ውስጥ የተጠቀመው ከ30 በመቶ እንደማይበልጥ ምንጮች ገልጸዋል፡፡

የልዑካን ቡድኑ ባምባሲ አካባቢ በሚገኘው በጀማፃና በጋሪቡ መተማ አካባቢ የሚካሄደውን የመንደር መሰባሰብና የመስኖ ፕሮጀክቶች ከጎበኘ በኋላ የሥራ አፈጻጸሙ ዝቅተኛ መሆኑን ደምድሟል፡፡

የክልሉን ፕሬዚዳንት አቶ አህመድ ናስርን ጨምሮ የክልሉ ሴክተር መሥርያ ቤቶች በተገኙበት በአሶሳ ከተማ በተካሄደው ስብሰባ ክልሉ ደካማ አፈጻጸም ማሳየቱ ተገልጿል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በዕድገት ወደኋላ የቀሩ ክልሎችን እንዲደግፉ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ትዕዛዝ የተሰጣቸው የትምህርት ሚኒስቴር፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መሥርያ ቤቶች የሚጠበቅባቸውን ድጋፍ እንዳልሰጡ መጠቆሙን መረዳት ተችሏል፡፡ በዚህ ስብሰባ በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ያለፉት ስህተቶች ታርመውና ሥራው ተካክሶ እንዲሠራ መመርያ ተሰጥቷል፡፡

በጋምቤላ ክልል ኦደግሞ የኦቦቦ መንደር ማሰባሰብና የላሬ ወረዳ መንደር ማሰባሰብ ሥራዎች ተጎብኝተዋል፡፡ በእነዚህ ጣቢያዎች የማስፈጸም አቅም ማነስ ቢኖርም፣ ለሥራው አፈጻጸም ዝቅተኛ መሆን ዋነኛው ተጠቃሽ ምክንያት የሆነው በ2004 ዓ.ም. በክልሉ ውስጥ የተፈጸሙ ሁለት ግድያዎች ናቸው፡፡ በርካታ ሰዎች ያለቁባቸው እነዚህ ግድያዎች የክልሉ አስፈጻሚ መሥርያ ቤቶች በሚፈልጉት ፍጥነት ሥራቸው ላይ እንዳያተኩሩ አድርገዋል ተብሏል፡፡

“የፀጥታ መደፍረስ አጋጥሟል” ሲሉ የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ጋት ሉዎክ የሥራ አፈጻጸሙ ዝቅተኛ የሆነበትን ምክንያት ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ የፀጥታ ችግር በማጋጠሙ የክልሉ ባለሥልጣናት አብዛኛው ጊዜያቸውን በዚሁ ጉዳይ ላይ አጥፍተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ክልሉ በጠየቀው መሠረት የፌዴራል መንግሥት ዘርፈ ብዙ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አቶ ጋት ሉዎክ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

መንግሥት በ2007 ዓ.ም. የሚጠናቀቀውን የምዕተ ዓመቱን የልማት ግቦችን ለማሳካት ዕቅድ መንደፉ ይታወሳል፡፡ ዕቅዱን ለማስፈጸም ከተያዙ አቅጣጫዎች መካከል በዕድገት ወደኋላ የቀሩ ክልሎች መሠረት ልማትን ለማሟላት አመቺ ባለመሆኑ ነዋሪዎች ተሰባስበው በመንደር እንዲቋቋሙ ማድረግ አማራጭ ሆኗል፡፡

 በዚህም ውኃ፣ ትምህርት፣ ጤናና የመንገድ መሠረተ ልማት ማሟላት ይጠበቅበታል፡፡  አቶ አዲሱ በዕድገት ወደኋላ የቀሩ ክልሎችን ለመደገፍ የተቋቋመውን ቦርድ የሚመሩ ሲሆን፣ አቶ ፀጋዬ ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደኅንነት ጉዳዮች አማካሪ ናቸው፡፡

የአንድ ለአምስት ፖለቲካዊ አደረጃጀት ወደ መንግስት መ/ቤቶች እየዘለቀ ነው

ኢሳት ዜና:- ግንቦት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
የፌዴራል የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ሠራተኞቹን አንድ ለአምስት በሚል አደረጃጀት በማዋቀር በሥራ ሰዓት ጭምር ስብሰባዎችን በማካሄድ ሠራተኛው እርስ በርስ እንዳይተማመን የማድረግ አሠራር ተግባራዊ በማድረጉ በሥራ ዋስትናቸው ላይ ከፍተኛ አደጋ መጋረጡን አንዳንድ ሠራተኞች አስታውቀዋል፡፡

ባለሥልጣኑ ከቅርብ ግዜ ወዲህ የልማት ሠራዊት ለመገንባት በሚል ሠራተኛው አንድ ለአምስት እንዲደራጅና በየዕለቱ ከ30 ደቂቃ ላላነሰ ግዜ በቀኑ ውስጥ ባጋጠሙ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት በሚል ሰበብ ስብሰባ እንደሚቀመጥ ሰማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ ሠራተኞች ተናግረዋል፡፡

በስብሰባዎቹ ላይ ለየት ያለ ኀሳብ ማቅረብ እንደማይቻል፣ከቀረበም “የአመለካከት ችግር አለብህ ወይም አለብሽ” የሚል ዛቻና ማሸማቀቅ የተለመደ ክስተት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ሠራተኞቹ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ አገራችንን በሙያችን ለማገልገል አስበን የተቀጠርን ቢሆንም ሳንወድ በግድ እንድንደራጅ ተደርጎ በየቀኑ የሚደረገው ስብሰባ ውጤት ለአለቆች የሚላክበት ሁኔታ መፈጠሩ የሥራ ዋስትናችንን አደጋ ላይ እንዲወድቅ ምክንያት ሆኗል ብለዋል፡፡

ባለሥልጣኑ ከሙስናና ብልሹ አሰራር ጋር በተያያዘ ሰራተኞች ከተጠረጠሩ የማባረረ ሥልጣን እንዳለው የጠቆሙት ሰራተኞቹ በአሁኑ ሰዓት ግን በፖለቲካ አመለካከት ብቻ ሰራተኞች ከሥራ የሚባረሩበት ሁኔታ እየተፈጠረ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡በዚህ ዓመት ብቻ ከ300 በላይ ሰራተኞች መባረራቸውንም በምሳሌነት አንስተዋል፡፡

በአቶ ጁነዲን ሳዶ የሚመራው የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ይህን ዓይነቱ አሰራር“የልማት ሠራዊት ” በሚል ስያሜ የሚጠራው ሲሆን በሁሉም የመንግስት መ/ቤቶች ተግባራዊ ለማድረግ አቅዶ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ በ2002 ዓ.ም በተካሄደው አገራዊ ምርጫ ይህ የአንድ ለአምስት አደረጃጀት ኢህአዴግን የ99 በመቶ ባለድል ካደረገው ወዲህ አደረጃጀቱ ለምርጫ ብቻ ሳይሆን ለልማትም መጠቀም አለብን በሚል አደረጃጀቱ ወደ መንግስት መ/ቤቶች ለማውረድ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡

ኢህአዴግ የ2002ን ምርጫ ለማስፈጸም ባወጣው የስትራቴጂ ወረቀት ላይ ፡“ …ከኢትዮጽያ ሕዝብ ውስጥ ከግማሸ በላይ የሚሆነው ዕድሜው ከ18 ዓመት በታች በመሆኑ የመራጩ ቁጥር ከ30 ሚሊየን በላይ ሊሆን እንደማይችል ይገመታል፡፡ከዚህ ውስጥ ቢያንስ አራት ሚሊየን ያህሉ የድርጅታችን አባል ነው፡፡

እያንዳንዱ አባል በቀላሉ ሊቀርባቸውና ሊያሳምናቸው የሚችል ቢያንስ አራት ወዳጆችና ዘመዶች አሉት ብንል እነዚህ ተደማምረው 20 ሚሊየን ይሆናሉ፡፡በእነዚህ ብቻ ቢያንስ 2/3 ኛውን ድምጽ ማግኘት ይቻላል…”ሲል የአንድ ለአምስት አደረጃጀትን ጠቀሜታ ገልጧል፡፡

በአሁኑ ሰዓት በመንግስት መ/ቤቶች ለማስረጽ እየተሞከረ ያለው የአንድ ለአምስት አደረጃጀት በሕዝብ ሐብትና ንብረት የኢህአዴግ ቀጣይ የምርጫ ድጋፍ ማሰባሰቢያ፣ አዳዲስ አባላትና ደጋፊዎችን የመመልመያ ስትራቴጂ እንጂ የልማት ጥማት አለመሆኑን አንዳንድ ወገኖች ከወዲሁ ሥጋታቸውን እየገለጹ ነው፡፡

ኢህአዴግ በምርጫ 2002 በ99 ነጥብ 6 በመቶ ማሸነፉን መግለጹ በአለም አቀፍ ደረጃ መሳለቂያ እንዳደረገው ይታወሳል።

Wednesday, May 23, 2012

ሚኒስትሩን የዘለፈችው ሙስሊም ወጣት፤ በደህንነቶች በደረሰባት አሰቃቂ ድብደባ ህይወቷ ማለፉ ተነገረ

ኢሳት ዜና:- ግንቦት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትሩን ስብሰባ ላይ የዘለፈችው ሙስሊም ወጣት፤ በደህንነቶች በደረሰባት አሰቃቂ ድብደባ ህይወቷ ማለፉ ተነገረ።ይህ አሳዛኝ ዜና ይፋ የሆነው፤የብዙሀኑ ሙስሊም አስተባባሪ  አካል የሆነው “ድምፃችን ይሰማ” ኮሚቴ ፦አሳዛኝ የግፍ ዜና”በሚል ርዕስ ያሰራጨው መረጃ  ነው።

በቅርቡ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የሙስሊሞችን ጥያቄ በተመለከተ ከየክፍለ-ከተማው ሰዎችን በመምረጥ ስብሰባ አካሂዶ እንደነበር ያወሳው ኮሚቴው፤በዚሁ ስብሰባ ላይ ከኮልፌ ክፍለ-ከተማ ሁለት ወንዶች እና ፍርዶስ የተባለች ወጣት  ሴት መሳተፋቸውን አመልክቷል።

ስብሰባውን ሲመሩ የነበሩት ሚኒስትሩ ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም  ብዙሀኑን ሙስሊም ያስተባብሩ ዘንድ በተመረጡት የኮሚቴ አባላት ላይ አስፀያፊ እና ድንበር ዘለል ንግግሮችን ሲደጋግሙ መደመጣቸውን የጠቀሰው ኮሚቴው፤የሰውዬውን ዘለፋና ስድብ መሸከም ያቃታት እህት ፍርዶስ የእልህ ሲቃ እየተናነቃት ሚኒስትሩን ዘልፋ የስብሰባ አዳራሹን ለቅቃ መውጣቷን አብራርቷል።

ከአዳራሹ ወጥታ በ አቅራቢያው ወዳቆመቻት ቶዮታ ቪትዝ የግል መኪናዋ በመግባት ወደመጣችበት ለመመለስ መንቀሳቀስ እንደጀመረች በሁለት ላንድክሩዘር መኪኖች የሞሉ ደህንነቶች ተከትለው በማስቆም እሷንም፤መኪናዋንም ይዘው መሰወራቸውን ኮሚቴው አጋልጧል። “ከዚያም እህታችን ፍርዶስን  በሚያሰቅቅ እና በሚዘገንን መልኩ በኤሌክትሪክ “ሾክ”እያደረጉ አቃጠሏት” ያለው ኮሚቴው፤በዚህም ምክንያት ወጣት ፍርዶስ ወዲያውኑ መናገርም፤መንቀሳቀስም ማቆሟን ገልጿል።

እንደ ድምፃችን ይሰማ መግለጫ፦ደህንነቶቹ በፍርዶስ ላይ የተጠቀሰውን የጭካኔ ድርጊት ከፈፀሙባት በሁዋላ  ከነ መኪናዋ መኖሪያ ቤቷ በሯ ላይ ጥለዋት ሄደዋል። በሁኔታው ከፍተኛ ድንጋጤ ላይ የወደቁት የፍርዶስ ቤተሰቦች ልጃቸውን ለመታደግ  ሩጫ መጀመራቸውን የጠቀሰው ኮሚቴው፤ሆኖም የደረሰባት ጉዳት እጅግ ከባድ በመሆኑ ጥራታቸው ሁሉ ከንቱ መቅረቱን ነው ያመለከተው።

በሆነው ነገር ልባቸው በሀዘን የደማው የፍርዶስ አባት  የልጃቸውን ህይወት ለማትረፍ ከፍተኛ ወጪ በማውጣት ለህክምና  ወደ ሳዑዲ ዐረቢያ ይዘዋት ቢሄዱም፤ ደህንነቶቹ ባደረሱባት የኤሌክትሪክ ቃጠሎ በርካታ አካሎቿ ከጥቅም ውጪ በመሆናቸው ወጣት ፍርዶስ እስከወዲያኛው ተሰናብታለች። የከፋው አሳዛኝ ነገር  የወጣት ፍርዶስ ህይወት ማለፉን ተከትሎ ወላጅ እናቷ  በደህንነቶች ታፍነው መወሰዳቸው ነው ይላል ኮሚቴው።

ወላጅ እናቷን አፍነው የወሰዷቸውም የፈፀሙት አሰቃቂ ግፍ እንዳይሰማባቸው ለማድረግ በማሰብ ነው ብሎ እንደሚያምን የድምጻችን ይሰማ ኮሚቴ ገልጿል። መምህር የኔሰው ገብሬ ፦”ፍትህ በሌለበት አገር መኖር አልፈልግም”በማለት ራሱን ማቃጠሉን ተከትሎ የደህንነት አባሎች ፦”መረጃ እንዳትሰጥ”በሚል እህቱን በመኖሪያ ቤቷ አፍነው ማስቀመጣቸው ይታወሳል።

ወጣት ፍርዶስ እሷን እና ጓደኞቿን  እላፊ እየተናገሯቸው የነበሩትን የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትሩን በንዴት  በመዝለፏ ሳቢያ  በኤሌትሪክ ሾክ እየተደረገች እንድትሞት መደረጉን የሰሙ እትዮጵያውያን፤ሰሞኑን ጋዜጠኛ አበበ ገላው ፦ጠቅላይ ሚኒስትር መለስን የተቃወማቸው ኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ባለ ስብሰባ ላይ ቢሆን ኖሮ ምን ሊያደርጉት ይችሉ እንደነበር መገመቱ ቀላል ነው ብለዋል። 

ኢሳት የሟቹዋን ቤተሰቦች ለማነጋገር አደረገው ጥረት አልተሳካለትም። የኢትዮጵያ መንግስትም በጉዳዩ ዙሪያ የሰጠው አስተያየት የለም።

Tuesday, May 22, 2012

New Muslim protests planned in Ethiopia

By Peter Heinlein, VOA
ADDIS ABABA - Unofficial committees within Ethiopia's 30-million strong Muslim community are organizing demonstrations to protest what they say is government interference in Islamic affairs. Tensions are rising as the government tries to preempt what it sees as the rise of a hardline strain of Islam. 

Worshippers arriving for Friday prayers at Addis Ababa's Awalia mosque found a notice posted at the entrance, which read: "They managed to get in through the back door before. Let's make sure it doesn't happen again." 

The notice was signed by a mosque committee opposed to what it says has been a quiet government takeover of Ethiopia's Islamic Affairs Supreme Council. The committee is demanding elections for new council members, to be held in the city's mosques. They rejected a suggestion that the vote be held in neighborhood government halls called kebeles.

"It should be inside the mosques, not in the kebeles because if it carried out in the kebeles there will be corruption, or some of the government authorities may participate. That is not fair. It is related to religion. There must not be interference of government in such tasks," he said. Standing at the entrance to the mosque, Ibrahim Hassan who teaches computer science at the Awalia Mission School, says holding the election in kebele halls would open the door to mischief.

Teacher Ibrahim accuses the council of trying to indoctrinate Ethiopian Muslims into the little known al-Abhash sect that preaches non-violence, as opposed to the more militant Salafist brand of Islam. Awalia mosque has been at the center of protests against what many Muslims see as government efforts to ban the teachings of the conservative Salafist sect of Islam. The Islamic Supreme Council recently fired several teachers at the Awalia mission school and shut down an Arabic language teaching center.

"They think that the committee may be terrorists," he said. "They consider us terrorists, but it represents all the Muslim communities. They said that [some] Salafists are members of al-Qaida, but in Ethiopia all of the Muslims are not members of al-Qaida, they are simply regular Muslims."Prime inister Meles Zenawi last month signaled a crackdown on those he accused of “peddling ideologies of ntolerance." In a speech to parliament, he said a few Salafis had formed clandestine al-Qaida cells in the southern part of the country.

Days later, our protesters were killed and many others injured in the southern state, Oromia when they tried to prevent police from arresting a Muslim cleric accused of promoting a radical ideology. Last week, five men, including one Kenyan national, were arraigned in Addis Ababa's federal court on charges of operating an al-Qaida cell out of a mosque in Oromia.

In another incident this month, Ethiopian authorities expelled two Arab men said to have been visiting from an unnamed Middle Eastern country. The two were detained after making what police called “inflammatory statements” and distributing materials at Addis Ababa's main Anwar mosque.

And last Friday, dozens of young men were reported to have stood outside Anwar mosque with tape over their mouths in a silent protest. Young men standing at the entrance to Awalia mosque at last Friday's prayers said another big demonstration is planned for this week. More than half of Ethiopia's roughly 90 million people are Christian, while an estimated 35 percent are Muslim. The Horn of Africa nation has long prided itself on its religious tolerance.

Valuable Reference
(Yuunis Hajji Mul'ataa)

ወጣቷ ህይወቷ አልፎ ገደል ውስጥ ተጥላ እና በአውሬ ተበልታ ተገኘች

በአዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ በተለምዶው መገናኛ በሚባለው አካባቢ ማንነትዋ ያልታወቀ ሴት ህይወቷ አልፎ በአካባቢው በሚገኝ ገደል ውስጥ ተጥላ፣ እንዲሁም በአውሬ ተበልታ በትናንትው ቀን መገኘቷን የፍትህ ዘጋቢ በቦታው ተገኝቶ ለመመልከት ችሏል፡፡

30 ዓመት እንደሚሞላት የተገመተችው ይህች ወጣት ትናንት አስከሬኗ የተገኘ ሲሆን ግድያው መቼ እንደተፈፀመና አስክሬኗም መቼ በስፍራው እንደተጣለ የታወቀ ነገር የለም። በቦታው የተገኘው የፍትህ ዘጋቢም አስክሬኑ የቆየ መሆኑን ለማየት የቻለ በመሆኑ ከፊል የሰውነት አካሏ በአውሬ መበላቱን አረጋግጧል።

ዘጋቢውም ስለሟቿ የበለጠ መረጃ እንዲሰጡት በአካባቢ የነበሩትን የፖሊስ አባላት ቢጠይቅም ፖሊሶቹ ‹‹ገና ነው… ምንም ስላላወቅን መረጃ ልንሰጥ አንችልም።›› በማለታቸው ያደረገው ሙከራ  አልተሳካም። ለህትመት እስከገባንበት ሰአት ድረስ ማንነቷን የሚገልፅና ዘመድ ነኝ ብሎ የመጣ አካል አለመኖሩን ለማወቅ ተችሏል።

Source: www.fetehe.com

በሰሜን ጐንደር ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ከሁለት ሺህ በላይ ገበሬዎች ከእርሻ መሬቶቻቸው ተፈናቅሉ ተባለ

 By www.fetehe.com
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ጐንደር ዞን ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ የሚኖሩ ከሁለት ሺህ በላይ ገበሬዎች ለአመታት እያረሱ ከሚያለሙት የእርሻ መሬታቸው በተለይ ከባለፈው ወር ጀምሮ በኢንቨስትመንት ሰበብ መፈናቀላቸውን የፍትህ ምንጮች ገለፁ።

ከስድስት እስከ አስራ አምስት ዓመት ያህል እንደያዙት የእርሻ መሬት ስፋት መጠን ለመንግስት  ተገቢውን ግብር በመክፈል መሬታቸውን በማልማት ይተዳደሩ እንደነበረ የሚናገሩት እነኚህ ገበሬዎች፣ የማፈናቀል ሂደቱ ከጀመረበት ከሶስት ወራት ወዲህ በአጠቃላይ መፈናቀላቸውን ምንጮች ያስረዳሉ። ለገበሬዎቹ መፈናቀል ዋናው ምክንያትም ከሌላ አካባቢ ለመጡ የሀገር ውስጥና የውጪ ሀገራት ኢንቨስተሮች መሬታቸው መሰጠቱ ነው።

‹‹ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ለመሬቱ ውል አልያዛችሁም ተብለናል። እኛ ደግሞ ውል ያልሰጣችሁን እናንተ ናችሁ የሚል መልስ ስንሰጣቸው ከአሁን በኋላ ለአዲስ ሰው እንጂ ለሌላ ለነባር አንሰጥም ተባልን›› የሚሉት አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የአካባቢው ነዋሪ ‹‹እየተሰራ ያለው ስራ ይዘገንናል›› በማለት ለፍትሕ ተናግረዋል።

‹‹እህል አብቃይና እህል የማያበቅል መሬት›› እየተባለ እንዲጠቀሙ ለተፈለጉ አካላት ጥሩ ቦታ፣ እንዲጠቀሙ ላልተፈለጉት ደግሞ ለእርሻ ስራ የማያመች መሬት ተለይቶ መስጠቱን ምንጮች በሃዘኔታ አስረድተዋል። ለአመታት ተገቢውን ህጋዊ ግብር የሚከፍሉበትን የእርሻ መሬት እየተነጠቁ ለባለሃብቶችና ለኢንቨስተሮች ሲሰጥ በተባለው መሰረት ምትክ ቦታ እንዳልተሰጣቸው ገበሬዎቹ ገልፀዋል።

ለችግራቸው መፍትሄ ለማግኘት የሰሜን ጐንደር መስተዳድር ጋር በተደጋጋሚ በመመላለስ የመስተዳሩ ኃላፊ የሆኑትን አቶ ግዛው አማረን ቢያነጋግሩም ‹‹አሁን ምንም እንዳትናገሩ፣ ሄዳችሁ ወረዳቸውን ጠየቁ›› የሚል መልስ ማግኘታቸውንና ወረዳውም ‹‹ዞኑን ጠይቁ›› እንዳላቸው ስማቸው እንዳይጠቀስ ያልፈለጉት የአካባቢው ነዋሪ ለፍትህ ተናግረዋል።

‹‹የዘንድሮ እርሻ ሊጀምር የቀረው ሶስት ወር ነው፡፡ ግብር ከምንከፍልበት መሬት ተፈናቅለናል፡፡ የአርማጭሆ ህዝብ እየተፈናቀለ ይገኛል፡፡ ህብረተሰቡ ከቀየው ከተነቀለ የት ሊሄድ እንደሚችል ማሰብ ነው›› በማለት ተፈናቃዮች ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ፍትሃዊ የሆነ የመሬት ክፍፍል ሊያገኙ እንደሚገባና አድሏዊ ስራ መስራቱ ሊቆም እንደሚገባ ያስገነዘቡት ምንጮች ‹‹የሚመለከተው አካል ለችግራቸው አፋጣኝ ምላሽ ሊሰጠንና መሬታችንን ሊመለስልን ይገባል›› በማለት በምሬትና በሀዘን ለፍትህ ተናግረዋል። 

የፍትህ ዘጋቢም ጉዳዩ ወደሚመለከተው ወደ ሰሜን ጐንደር አስተዳደር ቢሮ ስልክ ብንደውልም የቢሮው ስልክ ስለማይመልስ ምላሻቸውን ማካተት አልቻልንም።

ተቀናቃኝ ቡድኖችና ፖለቲካ

BY ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም
ተመስገን ደሳለኝ በተቀናቃኝ ቡድኖች ላይ አዲስ የመነጋገሪያ ርእስ ከፍቶአል (ግንቦት 3፣ 2004)፤ ጉዳዩ በጣም አንገብጋቢና በጣም ወቅታዊ ነው፤ እንደተለመደው አንብበን ችላ የምንለው ጉዳይ አይደለም፤ ሁላችንም በተቻለን መጠን እውነትን ይዘን ያለ ይሉኝታና ያለፍርሃት በራሳችን ላይ እንዝመትና እውነትን ይዘን እንነሣ።

በ1997 መኢአድ፣ ኢዴፓ፣ ኢዴሊና ቀስተ ደመና የሚባሉት የፖለቲካ ፓርቲዎች አንድ ሆነው ቅንጅትን ፈጠሩ፤ ነገር ግን የመኢአድን ከአቶ ኃይሉ ሻውል፣ ኢዴፓን ከአቶ ልደቱ ህልውና ለመለየት በፍፁም የማይቻል ሆነ፤ ስለዚህም የቅንጅትን ህልውና ፈተና ውስጥ ከተቱትና ተበታተነ፤ እስካሁን ድረስ ህልውናውን ከሕዝብ ህልውና ጋር አስተሳስሮ የቆየ የፖለቲካ ፓርቲ በኢትዮጵያ ውስጥ የለም፤ በገዢው ወንበር ላይ በጠመንጃ ኃይል ከወጡ በኋላ ጉልበትና ሀብት ሁሉም በጄ ሁሉም በደጄ ብለው ኢሰፓና ወያኔ/ኢሕአዴግ ሎሌዎቻቸውን ሰብስበው ፓርቲ ቢሉ ዋጋ እንደሌለው አይተናል፤ ደርግ በጉልበት ስልጣን በመያዙና ስልጣንን ጉልበት ብቻ በማድረጉ እንደተጠላ ተፍረክርኮ አይዞህ የሚለው ሳያገኝ ወድቆ ተበታተነ፤ ወያኔ/ኢሕአዴግ እንደገና በጉልበት ኢሰፓን ተካ፤ ሥልጣንን ጉልበት ብቻ አድርጎም እየገዛ ነው፤ በኢሰፓ ዘመን ተቀናቃኝ የፖለቲካ ፓርቲዎች በስምም በተግባርም አልነበሩም፤ በወያኔ/ኢህአዴግ ዘመን የፖለቲካ ፓርቲዎች በስም ተፈልፍለው በተግባር ተለጉመው በመኖና ባለመኖር መሀከል እያጣጣሩ አሉ፤ ያውም ምርጫ ቦርድ መልካም ፈቃዱ ሲሆን!

ለይስሙላ የተቋቋሙት ፓርቲዎች በምርጫ ጊዜ ትንሽ የተፈቀደላቸውን ያህል አባላት አስመርጠው በብሔራዊ ምክር ቤት (ፓርላማ) ያስቀምጣሉ፤ የተከበሩት አባላትም ቤትና ደመወዝ ያገኛሉ፤ የመጨረሻው ዓላማቸውም ይኸው ነው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች በስም ተሰይመው፣ ህልውናቸውን በአንድ ወይ በሁለት ሰዎች ስም ያስከብራሉ።

በወያኔ/ኢሕአዴግ ዘመን አንድ የተለመደ አጉል ፈሊጥ አለ፤ በሆነ ባልሆነው ወያኔ/ኢሕአዴግን መውቀር ያስመሰግናል፤ በአንጻሩ በተቀናቃኝ ቡድኖች ወይ በመሪዎቻቸው ላይ ትችት ማቅረብ እንደክህደትና ከኢትዮጵያዊነት መስመር እንደመውጣት ይታያል፤ ይህ በተደጋጋሚ የታየ ነው፤ በቅንጅት መሪዎች መሀከል የነበረውን የስልጣን ሽኩቻ በአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ስናገር በመጀመሪያ የራዲዮው ጠያቂ የነበረችው አነጋገሬን አልወደደችውም፤ የግል ስሜትዋን ለመግለጽ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ እንደገና ደውላ ተገቢ ያልሆነ ጥያቄ ጠየቀችኝ፤ ወሬው ከተላለፈ በኋላም ብዙ ሰዎች እየደወሉ ለብቻቸው ብታነጋግራቸውና ብትመክራቸው ይሻል ነበር በማለት የወቀሳ ትችት አቀረቡልኝ፤ እነዚህ ሰዎች የማከብራቸውና ሀሳባቸውን የማልንቅባቸው ናቸው፤ ለሁሉም የመለስሁላቸው እነሱ ለእኔ የሰነዘሩትን ምክር አንደኛ እኛ ሳናስብበትና ተግባራዊ ሳናደርገው ቀረን ብለው መገመታቸው የሚያሳዝን መሆኑን ነበር፤ ሁለተኛ ሁለትና ሶስት ወራት በማይሞላ ጊዜ ውስጥ በተዋናውያኑ በራሳቸው እውነቱ ገሀድ እንደሚወጣ ነግሬአቸው ነበር፤ እኔ የሥልጣን ጥሙን ሽኩቻ በማንሣቴ ለጠብ በር የከፈትሁ የመሰላቸው ሰዎች በቅንጅት ውስጥ የነበረውን ትግል የማያውቁ ናቸው፣ ገና ቀደም ብዬ ሌላው ሁሉ ካቃተኝ በኋላ የስልጣን ሽኩቻው ቅንጅትን እየጎዳው እንደሆነ ስለተረዳሁ ለቅንጅት ሊቀ መንበር ለኃይሉ ሻውል ደብዳቤ ጽፌ ከምክር ቤት መሰናበቴን አሳወቅሁ፤ ከቅንጅት ምክር ቤት ስወጣ በይፋ በአደባባይ ሳልናገር መቅረቴ ስሕተት ነው፤ መናገር ነበረብኝ፤ ግን ያው በኋላ ከብዙ ሰዎች የሰማሁት ወቀሳ በእኔም ውስጥ ስለነበረ ይሉኝታ ይዞኝ ተሳሳትሁ፤ ከቃሊቲ ከወጣን በኋላ በህንድ አገር ሀኪም ቤት ማጅራቴን በመጋዝ ለመተርተር ስዘጋጅ ድንገት ሳልነቃ ብቀር እውነት ተዳፍኖ እንዳይቀር በማለት ምስክርነቴን ሰጠሁ፤ በዚያን ጊዜ እኔ የነበርሁበትን ሁኔታ በትንሹም ቢሆን ለመገመት ከተቻለ ለእውነት በእውነት ከመመስከር ሌላ ዓላማ እንደማይኖረኝ ለመረዳት እንዴት እንዳስቸገረ እስከዛሬ አልገባኝም፤ ጥርጣሬያችንና አለመተማመናችን ድንበር የለውም ማለት ነው።

ከዚያ በኋላ ብዙ መጽሐፎች ተጽፈዋል፤ ገብረ ክርስቶስ ኃይለ ሥላሴ፣ ልደቱ አያሌው፣ ደበበ እሸቱ፣ አንተነህ ሙሉጌታ (የመጽሐፉን ርእስ አበላሽቶት ብዙ ሰዎች አላነበቡትም እንጂ በጣም ጥሩ መጽሐፍ) መስፍን ወልደማርያምም ጽፈዋል፤ አሁን ደግሞ ሲሳይ አጌና (ከውጭ እንደጋዜጠኛ ይሁን ወይስ የውስጥ መስሎ አላውቅም፤ ነገር ግን በራድዮ ሲናገር እንደሰማሁት ብርሃኑ ነጋን ከእውነቱ ሊያርቀው በጣም ሲሞክር እውነቱን ይደፈጥጣል)፤ ለማናቸውም ታዛቢዎች ተናገሩት አልተናገሩት በኃይሉ ሻውል፣ በብርሃኑና በልደቱ መሀከል የነበረውን ግልጽ የሆነ ሥርዓት ያጣ ፉክክር ማንም ሊክደው ወይም ሊያድበሰብሰውና ሊያልፈው አይችልም፤ ለምን ቅንጅት ፈራረሰ? አንዳንዶቻችን ክብራችንን አንጥፈን ለማስታረቅ ሞክረናል፤ አንድ ምሳሌ ለመስጠት በቀጠሮ ሄደን አቶ ገብረጻድቅ፣ አቶ ይልማ ይፍሩና እኔ ከአቶ ኃይሉ ሻውል አጥር ውጭ ለእኩል ሰዓት ያህል መኪና ውስጥ ቆይተን ሳይሆንልን ተመልሰናል፤ በኋላም አሜሪካ ሆኖ በነጭ ወረቀት ከሕግ ውጭ የሆነ የሹም-ሽር ሲያደርግ ሀሳቡን ለማስለወጥ አሜሪካ ስልክ ደውዬ ለማነጋገር ብሞክር እኔንም ባላንጣው አደረገኝ፤ ተፎካካሪዎቹን ለማቀራረብ፣ ለማስታረቅና ወደአብሮ መሰለፍ ለማምጣት በተደረገው ጥረት የተሳተፉትን ሁሉ ተፎካካሪዎቹ በጥላቻ ይመለከቱአቸው ጀመሩ።

በልደቱ የተጀመረው የቅንጅት መገነጣጠል፣ በብርሃኑ ነጋና በኃይሉ ሻውል ቀጥሎ ብርቱካን የምትመራው አንድነት ብቻውን ቀረ፤ በአንድነትም ውስጥ ገና ከመጀመሪያው ጠቅላላ ጉባኤ ጀምሮ ብርቱካን በመመረጥዋ ቅር ያላቸው አባሎች አኩርፈው ችግር ተፈጥሮ ነበር፤ ብርቱካን ስትታሰር ኤንጂነር ግዛቸው ሽፈራው በጉጉት ሲጠብቀው የነበረውን ወንበር አገኘና የአምባገነንነት አገዛዙን በግምባር ቀደምትነት ከዶር. ኃይሉ አርአያና ከአቶ ዓሥራት ጣሴ ጋር ጀመረ፤ ሁሉም ቢያንስ ከሁለት ሺህ ብር በላይ የወር ደመወዝ ያገኙ ነበር፤ እንዲሁም የጽሕፈት ቤቱ ሠራተኞች ሁሉ በጥሩ ደመወዝ ተሰንገው የተያዙ ነበሩ፤ እነዚህ ናቸው ሎሌዎች አይደለንም የሚሉት፤ ከበስተጀርባቸውም የብሔራዊ ምክር ቤት ገብተው ሌሎቹ ቃሊቲ በነበሩበት ጊዜ ደመወዝ ሲበሉ የነበሩ ናቸው፤ ያንን የደመወዝ ወንበር እንደያዙ ለመቀጠል የተመኙ የአንድነት የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴና የምክር ቤት አባላት ነበሩ፤ ግዛቸው እነዚህን ሁሉ ሎሌዎች አሰልፎ ስሙ ወደምግባሩ መራውና የማይበገር አንባ-ገነን ሆነ፤ ከመጀመሪያዎቹ አወዛጋቢ ጉዳዮች መሀከል አባላት በጽሕፈት ቤቱ አዳራሽ ያለፈቃድ እንዳይሰበሰቡ፣ ግዛቸው፣ ኃይሉ አርአያና ዓሥራት ባልፈቀዱት ጉዳይ መወያየት መከልከሉን፣ በነፃነት አባልነታቸውን ለመወጣት የሚፈልጉትንና ከሎሌነት ያፈነገጡትን ሰዎች ለማስወንጀል ማስፈራራት ነበሩ፤ ከውጭም ድጋፍ ነበራቸው፤ የቅንጅት የድጋፍ ኮሚቴ በአሜሪካ ሊቀመንበር ነኝ የሚል አክሎግ ልመንህ የሚባል የማስፈራሪያ ደብዳቤ ጽፎልን እኔ መልስ ሰጥቸውአለሁ፤ ሌሎች አንገብጋቢ ጉዳዮች ዋና ጸሐፊው አቶ ዓሥራት ጣሴ አንደኛ አንዲት ጸሐፊ የነበረች የአንድነት አባልን ያለማስጠንቀቂያና ካሣ፣ ሁለተኛ አንዲት የጽዳት ሠራተኛን እንዲሁም ያለምንም ማስጠንቀቂያና ካሣ ከሥራ ማስወጣቱ ናቸው፤ በነዚህ ምክንያቶች አንድነት ለሁለት ተከፈለ፤ ግዛቸው መርጠው ወንበሩ ላይ ያስቀመጡትን ሰዎች አባርሮ በዶር. ነጋሶ ጊዳዳ፣ በአቶ ስዬ አብርሃና በአቶ ገብሩ ዓሥራት ድጋፍ መሰላሉን ሊወጣ ተመኘ፤ መሰላሉ ወደቀ።

ዛሬ ቅንጅትን ሰባብረው ግልገል የሥልጣን ፈረሶችን የፈጠሩት ሁሉ በሦስት ምክንያቶች ኮስሰዋል፤ አንደኛ ሰውን መግዣ ገንዘብ እያነሰ ነው፤ ሁለተኛ አባሎችም የተሻለ ንቃትና ትምህርት እያገኙ ሎሌነትን እምቢ እያሉ ነው፤ ሦስተኛ የኢትዮጵያ ሕዝብ የአዲሶቹን መኳንንት የኤንጂነር ግዛቸውን፣ የዶር. ኃይሉ አርአያንና የአቶ ዓሥራት ጣሴን ‹‹በታላላቅ›› ሰዎች ጥላ ስር ሆነው ለመሽሎክ ያቀዱት አልተሳካላቸውም፤ መማር የሚችሉት ሊማሩ ሄዱ፤ የማይችሉት ቀሩ።

Ethiopian Government, Muslims Clash about Ideology

By Peter Heinlein,,VOA
ADDIS ABABA - Unofficial committees within Ethiopia's 30-million strong Muslim community are organizing demonstrations to protest what they say is government interference in Islamic affairs. Tensions are rising as the government tries to preempt what it sees as the rise of a hardline strain of Islam.

Worshippers arriving for Friday prayers at Addis Ababa's Awalia mosque found a notice posted at the entrance, which read: "They managed to get in through the back door before. Let's make sure it doesn't happen again."  The notice was signed by a mosque committee opposed to what it says has been a quiet government takeover of Ethiopia's Islamic Affairs Supreme Council.  The committee is demanding elections for new council members, to be held in the city's mosques.  They rejected a suggestion that the vote be held in neighborhood government halls called kebeles.

Standing at the entrance to the mosque, Ibrahim Hassan who teaches computer science at the Awalia Mission School, says holding the election in kebele halls would open the door to mischief. "It should be inside the mosques, not in the kebeles because if it carried out in the kebeles there will be corruption, or some of the government authorities may participate.  That is not fair.  It is related to religion.  There must not be interference of government in such tasks," he said.

Awalia mosque has been at the center of protests against what many Muslims see as government efforts to ban the teachings of the conservative Salafist sect of Islam.  The Islamic Supreme Council recently fired several teachers at the Awalia mission school and shut down an Arabic language teaching center.  Teacher Ibrahim accuses the council of trying to indoctrinate Ethiopian Muslims into the little known al-Abhash sect that preaches non-violence, as opposed to the more militant Salafist brand of Islam.

"They think that the committee may be terrorists," he said. "They consider us terrorists, but it represents all the Muslim communities.  They said that [some] Salafists are members of al-Qaida, but in Ethiopia all of the Muslims are not members of al-Qaida, they are simply regular Muslims."

Prime Minister Meles Zenawi last month signaled a crackdown on those he accused of “peddling ideologies of intolerance."  In a speech to parliament, he said a few Salafis had formed clandestine al-Qaida cells in the southern part of the country. Days later, four protesters were killed and many others injured in the southern state, Oromia when they tried to prevent police from arresting a Muslim cleric accused of promoting a radical ideology.

Last week, five men, including one Kenyan national, were arraigned in Addis Ababa's federal court on charges of operating an al-Qaida cell out of a mosque in Oromia. In another incident this month, Ethiopian authorities expelled two Arab men said to have been visiting from an unnamed Middle Eastern country.  The two were detained after making what police called “inflammatory statements” and distributing materials at Addis Ababa's main Anwar mosque.

And last Friday, dozens of young men were reported to have stood outside Anwar mosque with tape over their mouths in a silent protest.  Young men standing at the entrance to Awalia mosque at last Friday's prayers said another big demonstration is planned for this week.

More than half of Ethiopia's roughly 90 million people are Christian, while an estimated 35 percent are Muslim.  The Horn of Africa nation has long prided itself on its religious tolerance.

Opposition criticises Ethiopia-Sudan extradition agreement

By Tesfa-Alem Tekle. Sudane Tribune
May 21, 2012 (ADDIS ABABA) - Ethiopia’s biggest coalition of opposition parties, the Forum for Democratic Dialogue in Ethiopia (Medrek), has condemned a judicial agreement signed between Ethiopia and Sudan.
Last Wednesday, the two East African neighbours signed an agreement on the extradition of criminals intending to jointly battle crime, to enhance regional peace and promote justice in general. Ethiopian opposition politicians, however, doubt the new agreement is meant to only fight criminals and argue could have another hidden agenda.

Merara Gudina, the Medrek chairman and member of the Oromo People’s Congress (OPC), told Sudan Tribune on Monday that the convicts exchange agreement between Khartoum and Addis Ababa could be a special arrangement to prosecute political refugees. According to Gudina, the fresh judiciary accord is a cover to hand over exiled opposition politicians.

“In countries like Ethiopia where there is a dictatorial rule, being an opposition member is considered as being a criminal”, the opposition official told Sudan Tribune. He further said the agreement, if sued to target political refugees, will eventually ruin ties of the two people and would leave a “dark spot” on the history of the two countries.

A considerable number of Ethiopian opposition members sought refuge in Sudan after the 2005 election when post-election violence led to the killing of over 200 street protesters and to the arrest of hundreds of supporters and dozens of opposition figures. Earlier this year, an exiled Ethiopian human rights group, the Berlin-based Solidarity Committee for Ethiopian Political Prisoners (SOCEPP), accused the Sudanese government of further intensifying a crackdown against Ethiopian political refugees.

The group then alleged that Sudanese police have raided houses and rounded up dozens of Ethiopians in Omdurman and many parts of the capital, Khartoum, for forcible deportation. Last year, SCOEPP similarly accused Sudanese authorities of deporting former Ethiopian opposition politician, Andualem Alemayo, from Khartoum’s Kober prison, after he entered the country from neighbouring Eritrea.

The group has repeatedly urged the Khartoum government to refrain from forcibly deporting Ethiopian political refugees arguing they would risk prosecution back home by the government in Addis Ababa. The latest accord between Sudan and Ethiopia comes following another security agreement signed last December between the two countries not to harbour rebel figures or host each other’s rebel forces in their territory – an agreement aimed to enhance border security of the two countries and cripple any attempt of subversive and military activities of rebel groups on both sides.
(ST)

ወደ ኢትዮጵያ ሄደው ዘመዶቻቸውን ለመጠየቅ የፈለጉ ኢትዮጵያውያን ቪዛ እየተከለከሉ ነው

ኢሳት ዜና:- ግንቦት ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ወደ  ኢትዮጵያ ሄደው ዘመዶቻቸውን ለመጠየቅ የፈለጉ በርካታ ኢትዮጵያውያን፦”የግንቦት 7 አባላት ናችሁ” እየተባሉ በየ አገራቱ ባሉት የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች እየተከለከሉ ነው። በቤልጂዬም የምትኖር እና ስሟን መግለጽ ያልፈለገች አንዲት ኢትዮጵያዊ ሰሞኑን ወደ አገሯ አቅንታ ዘመዶቿን ለመጠየቅ ብትፈልግም፤በብራሰልስ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፦”የግንቦት ሰባት አባል  ስለሆንሽ ቪዛ አንሰጥሽም” በማለት ከልክሏታል።

ኤምባሲው  ለአክቲቪስቷ የግንቦት ሰባት አባልነት የጠቀሰውና ያቀረበው ማስረጃ  በተለያዩ ጊዜያት ኢትዮጵያውያን ባካሄዷቸው የተቃውሞ ሰልፎች ላይ መሳተፏን ነው። እንዲሁም  በፍራንክፈርት፣ በዋሽንግተን ዲሲ እና በሌሎች የ አውሮፓ እና የአሜሪካ ከተሞች የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን ወደ አገር ቤት ለመሄድ ፈልገው ከየኤምባሲዎች  ተመሣሳይ ምላሽ ተሰጥቷቸው ቪዛ መከልከላቸውን ተናግረዋል።

የአቶ መለስ መንግስት ፦”የተቃውሞ ሰልፍ ማድረግ ህገ-መንግስታዊ መብት ነው” የሚል ህገ መንግስት ያረቀቀና ያጸደቀ ቢሆንም፤በተግባር እየተከተለ ያለው አገዛዝ፦”ንጉስ አይከሰስ፤ሰማይ አይታረስ” በሚል ያረጀ ብሂል የሚመራ  እንደሆነ ብዙዎች ይስማማሉ። ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም፦”የ ኢትዮጵያ ህገ-መንግስት የተፃፈበትን ወረቀት ያህል ዋጋ አላወጣም”ማለታቸው አይዘነጋም።


Monday, May 21, 2012

The Ethiopian Engima

Ben Rawlence, Senior Researcher, Africa Division, Human Rights Watch   

Mariam was painfully thin. Several of her 13 children peered out from behind her with hollow eyes. "I am trying to save my children. We are not living. We are subhuman," she told me. Food aid was available in her village in Southern Ethiopia. But not for her children. Her husband belonged to the wrong political party. The same month I was interviewing this desperate mother in 2009, President Obama was telling Ghana's parliament that: "Africa doesn't need strongmen, it needs strong institutions."

 Meanwhile, Prime Minister Meles Zenawi, one of Africa's longest serving strongmen, was using food aid as a weapon against opposition supporters, locking up opponents and journalists, and shutting down media and civil society organizations that reported on Ethiopia's slide into authoritarianism. In 2010, his party unsurprisingly won over 99 percent of the seats in parliament. On May 19, President Obama will welcome Prime Minister Zenawi to the G-8 summit at Camp David to discuss food security in Africa along with the democratically elected leaders of Benin, Ghana, and Tanzania. 

The invitation to Meles demonstrates that whatever the Obama administration has learned from the Arab Spring, it doesn't apply to Africa. It should. Cosseting autocratic regimes rarely ends well for anybody. Mariam wanted me to tell the world that their aid dollars were being misused. In a 2010 report, "Development without Freedom," we did. Yet the Ethiopian enigma is curious: the more repressive Ethiopia gets, the more aid it receives from Western governments. Why does a country with a human rights record rivaling those of repressive Sudan, Uzbekistan, or Zimbabwe enjoy such solid support in the U.S. and Europe? 

Since the 2010 elections Meles's government has detained dozens, and possibly hundreds, of opposition members, perceived opposition supporters, and others. No one knows exactly how many people have been arrested because no independent organizations have access to all of Ethiopia's known and secret detention facilities, where torture and ill treatment are common. There are few Ethiopian human rights groups to investigate the detentions because in 2009 Ethiopia passed a law on non-governmental organizations that strangled most local human rights groups by cutting off foreign funding. And the government has regularly detained and deported journalists who try to access the embattled Ogaden region, successfully cutting off news of the situation.

Of course Ethiopia is a reliable partner on counter-terrorism and regional security and perceived to be an oasis of stability amid Eritrea, Sudan, and Somalia. Ethiopia has held terrorism suspects from Somalia and Kenya for interrogation and hosts a U.S. drone base for operations in Somalia. Ethiopia intervened in Somalia in 2006 to oust the militant Union of Islamic Courts and deployed peacekeepers in the contested region of Abyei between Sudan and South Sudan. 

But the security partnership is not the only reason. Ethiopia appears to be making strong progress on meeting development goals, and donor partners such as the World Bank are anxious to sustain their "investments." Yet the proportion of the population requiring food aid remains stubbornly high and the numbers of Ethiopians fleeing the country due to repression or in search of economic opportunities they can't find at home are exploding. 

As long as Ethiopia appears to be making progress toward the United Nations' Millennium Development Goals, donors seem to care little about how that progress is achieved. Ethiopia even used some foreign-funded development programs to cement the ruling party's grip on power. As Mariam and many other people we interviewed told Human Rights Watch the ruling party discriminates against anyone it perceives as an opponent: access to donor-funded government services, food aid, housing, employment, promotions, educational opportunities, and land have all been used to encourage support for the ruling party. 

The government is pursuing controversial resettlement programs, indirectly supported by foreign assistance, forcing people to leave their ancestral lands and in some cases leaving them worse off. It has also expropriated vast tracts of land and forced resettlement of indigenous communities in the Omo valley, a UNESCO World Heritage site, to make way for state-run sugar plantations. Meanwhile the government has steadily whittled away what's left of the independent media. According to the Committee to Protect Journalists, more journalists have fled Ethiopia in the last decade than any other nation. 

This month, PEN American Center awarded its prestigious Freedom to Write award to Eskinder Nega, who is fast becoming Ethiopia's best-known journalist. Eskinder is in jail for the seventh time, but this time he is charged under a 2009 counterterrorism law that, so far, has primarily been used to target opposition leaders and journalists. Fifteen other journalists and opposition members have already been convicted (or charged) under the law, including two Swedish journalists who attempted to report on abuses in the Ogaden region.

Before Zenawi's government deported me for reporting on the politicization of aid, Eskinder Nega told me that he thought President Obama's Ghana speech heralded a new era for democratic governance in Africa. If Eskinder was right then, instead of inviting undemocratic leaders like Zenawi to Camp David, the Obama administration would review its approach to Ethiopia and call on the government to reverse its assault on human rights and democracy. But I fear that when Eskinder hears of the visit in his cell in Kaliti prison, he will know that his faith in President Obama's words was wrong.

Ben Rawlence is a Senior Researcher in the Africa Division at Human Rights Watch.

Read more